የኢትዮጵያ ብሎጎች ምን ጻፉ ከሚያዚያ 29 እስከ ግንቦት 6

አለማየሁ ገላጋይ እና በውቀቱ ስዮም በሳምንታዊው የፍትህ ጋዜጣ ላይ ስለኢትዮጵያና ጃፓን፣ ስለአጼ ቴዎድሮስና ስለአንድ የጃፓን ንጉሥ ክርክር ማካሄድ ከጀመሩ ሰንበትበት ብለዋል:: እኔም ሳምንት በመጣ ቁጥር የነዚህን ጸሀፍት ክርክር ለማንበብ መናፈቅ ጀምሪያለሁ:: ምንም እንኳ በውቀቱ በዚህ ሳምንት ክርክሬን አብቅቻለሁ ቢልም ሳምንትአለማየሁ ምን ሊመልስ እንደሚችል ለማወቅ ግን መጓጓቴ አልቀረም:: ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማሪያም ግን እንዲህ ያሉትን ያደባባይ ክርክሮች በተመለከት “በፍትሕ ጋዜጣ ላይ ለምንጽፍ ሁሉ እየተናገሩ አለማነጋገር፣ እያሰቡ አለማሳሰብ” በሚል ርእስ አንድ ጽሁፍ አስነብበዋል:: ይህቺ ጽሁፋቸው በብሎጋቸው ታትማ ስለነበር የዚህ ሳምንት የብሎግ ክለሳዬ ፊትአውራሪ አድርጊያታለሁ:: አንድ አንቀጽ ላቃምስና ወደ ሌሎች ብሎጎች ልለፍ::

“ሀሳብን በጋዜጣ ማውጣት አደባባይ መውጣት ነው፤ አደባባይ የሚወጡበት ጉዳይ የግል ሳይሆን የአገርና የሕዝብ ነው፤ መሆን አለበት፤ አደባባይ በወጣው ጉዳይ ላይ በአገርና በህዝብ ጉዳይ ያገባኛል የሚል ዜጋ ሁሉ ባለቤት ሊሆንበት ይችላል፤ በባለቤትነት ሊተችበት ይችላል፤ በጉዳዩ ላይ የሞቀ ክርክር ቢደረግበት ሁላችንም በብዙ መንገድ ተጠቃሚዎች ልንሆን እንችላለን፤ ነገር ግን እስከዛሬ የሚታየው አዲሱ ልምድ ከላይ ባለስልጣኖች እንደልባቸው ይናገራሉ፤ በግድም ይሁን በውድ አብዛኛው ሰው ይሰማቸዋል፤ ባለሥልጣኖቹን በማስተጋባት ቴሌቪዥኑና ራዲዮው ደጋግመው እስቲሰለች ድረስ ያሰማሉ፤ በግድም ይሁን በውድ የባለሥልጣኖቹ ንግግር ለብዙ ሰዎች ጆሮ ይደርሳል፤ ግን ጆሮ የደረሰ ሁሉ ወደልብ መተላለፉን እርግጠኛ መሆን አይቻልም፤ በአንጻሩ በግል ጋዜጦች ላይ የሚወጡት የተለዩና የተለያዩ ሀሳቦች በተለያዩ ጉዳዮች ላይ አመራሩን የሚተቹ ናቸው፤ እነዚህን ጋዜጦች የሚያነብቡ በጣም ጥቂቶች ናቸው፣ ጋዜጦቹን የሚያገኙዋቸው በገንዘባቸው እየገዙ በመሆኑ የሰዎችን ቀልብ መሳባቸው ይታወቃል፤ እነዚህን ትችቶች ባለሥልጣኖቹ ጉዳያቸው አድርገው የሚያነቡዋቸው አይመስለኝም፤ የእነሱ ንቀት ሚስትህ አረገዘች ወይ ቢሉት፣ ማንን ወንድ ብላ! እንዳለው ነው መሰለኝ፤ ባለሥልጣኖቹ ሁለት ጥቅሞችን ያጣሉ፤ አንደኛ የተቺዎቹን ሀሳብ መረዳትና ከራሳቸው ሀሳብ ጋር የማመዛዘን ዕድሉ ያመልጣቸዋል፤ ሁለተኛው ሕዝቡ በነፃነትና ያለምንም ግዴታ ትችቱን በማንበቡ ብቻ የሚያስተላልፈውን መልእክት ሳያውቁት ይቀራሉ፤ የዚህ ውጤት የአገር ጉዳት ነው፤ እንግዲህ እነሱ የሚናገሩትን ይናገራሉ፤ ሌላውም የሚናገረውን ይናገራል፤ በሁለቱም ወገን የሚነገረው ስለአንድ አገርና ስለአንድ ሕዝብ ነው፤ በሁለቱም በኩል የተያዘው ፈሊጥ ሳያነጋገሩ መናገር ነው፤ ክፉ ሕመም ነው።”

ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ጠቅ ማድረግ በቂ ነው:: አልያም ያለፈውን ሳምንት ፍትህ ጋዜጣ ማንበብ::

ቀጠልኩ ሰሞኑን ሀገራችን የአለም ኢኮኖሚ ፎረምን አስተናግዳ ነበር:: ፎረሙ ብዙ ገጽታ ነበረው። ኢትዮጵያ እያሳየች ባለው ኢኮኖሚያዊ መነቃቃት የተነሳ የዚህ ፎረም አዘጋጅ እንድትሆን ተመርጣለች በመባሉ በርካታ ኢትዮጵያውያን ስሜታቸውን ገልጽዋል:: የተደሰቱ ያልተዋጠላቸው እና ምንም ያልመሰላቸው ወይም ያልሞቃቸውም ያልበረዳቸውም ይገኙበታል:: ነገር ግን አቤ ቶክቻው ለማተኮር የፈለገበት ነጥብ በፎረሙ የሀገራት መሪዎች ውይይት ወቅት ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ የተናገሩት ላይ ነው:: አቤ ለጠቅላይ ሚንስትሩ ሽሙጣዊ ሰላምታ ባቀረበበት ብሎጉ ውይይቱ ላይ የነበረውን ድባብ በሚከተለው መልኩ አቅርቧል:: አንድ አንቀጽ እንካችሁ::

ማንም ያልደፈርዎትን ሰውዬ ትላንት በአለም ኢኮኖሚ ፎረም መድረክ ላይ፤ “ዲሞክራሲን ከሚያፍኑ እንደ ቻይናን ከመሳሰሉ ሀገራት ጋር በይበልጥ የመተባበራችሁ ምስጢር ምንድነው?” ብሎ ሲያበቃ “አቶ መለስ ዙሪያ ጥምጥም ሳይሄዱ በቀጥታ ይመልሱልኝ” ማለቱን ስሰማ እንዴት ቢደፍራቸው ነው? ብዬ የደነገጥኩትን መደንገጥ የተበሳጨሁት መበሳጨት አይጠይቁኝ። ለነገሩ ግን እርስዎም እኮ ራስዎን አለቅጥ ለተቺ አጋለጡ። ትዝ ይልዎት እንደሆነ፤ በፎረሙ ላይ አወያይ የነበረችው ሴት አንድ ጥያቄ ጠይቃዎ ያልተጠየቁትን ሲያወሩ፣ ሲያወሩ፣ ሲያወሩ ቆይተው ሰዓቱን ከፈጁት በኋላ፤ “ጥያቄሽን ረሳሁት ምን ነበር ያልሽኝ?” ብለው ድጋሚ ሲጠይቁ ተሰባሳቢው በሙሉ እንዴት እንደሳቀብዎ እኔም እንዴት እንደተሸማቀኩልዎ ቢያዩኝ ለአንዱ ቀበሌ ሊቀመንበር ያደርጉን ነበር።

ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ጠቅ ያድርጉ:: ከዚህ ጋር በተያያዘ የጠቅላይ ሚንስትሩ በውይይቱ ወቅት የሰነዘሯቸው አስተያየቶች በሌሎች አለም አቀፍ ብሎጎች ላይም ወጥተው ነበር::በተለይ አፍሪካ ውስጥ ስለተንሰራፋው ሙስና ተጠያቂው ምእራባዊያን ኢንቪስተሮች ናቸው የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት ፈጣን ብቻ ሳይሆኖ ፍትሀዊ ነው ለኢኮኖሚ እድገት ዲሞክራሲ ወሳኝ አይደለም የሚሉት አስተያየተያየቶቻቸው ሰፋ ያለ ትኩረት አግኝተው ነበር:: የጠቅላይ ሚንስትሩን አስተያየቶች እና ውይይቱን በከፊል እዚህ ትይይዝ ላይ ጠቅ በማድረግ ማግኝት ይችላሉ::

ጠቅላይ ሚንስትሩ እነኝዚህን አስተያየቶች ይስጡ እንጂ ብሎገሮች/ጦማሪያን በሳቸው አስተያየቶች አይስማሙም እንዳውም ዲ ብራሀን የተሰኝ በእንግሊዝኛ የሚታተም ብሎግ የጠቅላይ ሚንስትሩን አስተያየት የሚያፋልስ ሰፋ ያለ ጥናታዊ መልክ ያለው ትንታኔ አትሟል:: ከክርክሩ ባሻገር የዲሞክራሲን እና የኢኮኖሚ እድገትን ግንኙነት ግንዛቢዮዎትን ለማዳበር የሚረዳ ጽሁፍ ነው:: እዚህ ላይ ጠቅ በማድረግ ጽሁፉን ያንብቡት:: ኢኮኖሚው አደገ ተመነደገ የሀብት ክፍፍልም ፍትሀዊ ሆነ ኢትዮጵያም የማር እና የወተት ምድር ሆነች ለሚሉ ወገኖች ስኳር እንኳ ማግኝት እንዴት እንደቸገረው ስኳር እንደገና በሚለው ጽሁፍ ተስፋዪ አለማየሁ አትቷል። ጽሁፉን እዚህ ላይ ጠቅ በማድረግ ያንብቡት።

ስለ ሰዎች ስንሰማ እንዴት መስማት እንዳለብን ሦስቱ ማጣርያዎች በሚል ርእስ ስለ ሃሜት ክፋት ያስነበበን ዳንኤል ክብረት ነው:: ጽሁፉን እዚህ ላይ ጠቅ በማድረግ ያንብቡት። ባለፈው ሳምንት ስለ አብዮት ያስነበበን በፍቄ በዚህ ሳምንት ደግሞ የጋንዲ፣ ኪንግ እና ማንዴላ መንፈስ በሚል ርእስ እኛ ኢትዮጵያውያኖች ከነእዚህ የዓለም ሃብቶች አንፃር ራሳችንን አይተነው እናውቅ ይሆን? ብሎ እራሳችንን እንድንጠይቅ የሚገፋፋ ጽሁፍ አሥነብቧል:: ጽሁፉን ትይይዙን ጠቅ በማድረግ ያንብቡት።

ወደው እና መርጠው ኢትዮጵያዊ ስለሆኑ የውጪ ሀገር ዜጎች እና ስራዎቻቸው ያስነበበን ደግሞ ዘላለም ማልኮም ክብረት ነው:: ምንም እንኳ ዘላለም የእንግሊዝኛ ጦማሪ ቢሆንም ያነሰው ርእሰ ጉዳይ ከኢትዮጵያውያ ጋር የጠበቀ ግንኙንት ስላላቸው የውጪ ሀገር ዜጎች ስለሆነ በዚህ የአማርኛ ጦማር ክለሳ ውስጥ ላካትተው ግድ ብሎኛል:: ዘላለም የውጪ ሀገር ዜጎች ስለ ኢትዮጵያ ምን ያስባሉ የሚለውን ለመረዳት አስፈላጊ ናቸው ብሎ ያመነባቸውን አስር ፊት አውራሪ ምሁራን አቅርቧል:: ከነዚህም መሀከል ጀምስ ብሩስ ክርስቶፎር ክላፍም ዶናልድ ሊቭይን ክላውድ ሰምነር ይገኙበታል:: ሁሉንም ዝርዝር ለማግኝት ትይይዙን ጠቅ በማድረግ ያንብቡት።

ባለፈው ሳምንት አንድ የስነጽሁፍ ብሎግ አስተዋውቄ ነበር:: : ቤዋዬን:: ይህ ብሎግ በዚህ ሳምንት ደግሞ እውነት ቀመስ ልቦለድ አስነብቧል::ታሪኩ ስለስደት ነው:: አሳዛኝ ግን የበርካታ ኢትዮጵያውያን የህይወት እውነታ ታሪኩን ትይይዙን ጠቅ በማድረግ ያንብቡት።

አትሌቲክስ ለምትወዱ የፍሰሀ ተገኝ ብሎግ አመታዊው የዳይመንድ ሊግ አትሌቲክስ ውድድር ኳታር ዋና ከተማ ዶሀ ውስጥ ሲከፈት የተለያዩ አስደናቂና ያልተጠበቁ ውጤቶች ተመዝግበውበታል ይለናል:: ሀተታውን ለማንበብ እዚህ ጋር ጠቅ ያድርጉ:: መልካም ሳምንት::

Addis Ababa is hosting World Economic Forum. Does anyone care?

When Addis Ababa hosts the 22nd World Economic Forum for the first time on Africa soil will anyone care?

Oh sure there are some who cares and obviously their favorite theme in the media in the wake of World Economic Forum in Addis Ababa is Ethiopia’s speedy economic growth.

Before we go in to details of things, let me explain how free and independent media encourage economic growth. It has been said a thousand times that a free and independent media has played a great role in promoting economic development by solving primary problems of a certain society through the free flow of information. Furthermore a free media improves public policy implementation, by increasing government accountability and transparency and it also raise political consciousness of citizens. Definitely today’s global economic powers with the exception of may be China are primarily managed to grow because they have had comparatively free media.

I strongly believe that one topic that should be tackled in numerous debates in the forum should be the role of free and independent media and economic growth in Africa. Also other topics on the agenda should be issues like journalists’ incarceration, telecom services control by government and may be corruption. In fact the present spotlight of media on Ethiopia’s economic breakthrough is distracting attention from many serious challenges that Ethiopia’s free media is facing on day to day basis.

Free media gloom

The forum has started on Wednesday, however, does not promise well.

The forum has started on Wednesday after lots of bad news about Ethiopia’s free press five journalists—Woubshet Taye, Elias Kifle, Re’eyot Alemu and two Swedish journalists — sentenced to at least 10 years and more behind bars and 2012 PEN America press freedom award winner, Eskinder Nega, could face the death penalty if convicted this Friday. Even more worrying news is that government has triggered a reminiscence of a ‘Derg’ regime by reactivating highly restrictive directive that authorizes publishers to censor the content of newspapers. These are dire warnings that Ethiopia’s media is in a danger zone.

Ethiopia is dubbed as the Africa’s fastest-growing economies and I do not have a problem with that though the rate of the growth is questionable one. However Ethiopia’s political integration is inadequate and it lags behind its much heralded economic growth. National consultations mechanisms stay behind and even weaker than economic growth wise slow paced African countries for instance Zimbabwe. Differences persist over whether a liberal democracy, social democracy or even narrower version of democracy called revolutionarily democracy should prevail in Ethiopia.

There are no the slightest hints that this mood in Ethiopia could turn, though many press freedom activists campaigning for more freer environment during the past few weeks I have started to feel much more pessimist about Ethiopia’s press. And of course World Economic Forum hasn’t captured my imagination and many friends of mine in the way other similar meetings has. Will you care?

የኢትዮጵያ ብሎጎች ምን ጻፉ ከሚያዚያ 21 እስከ 29

የእስክድር ነጋን መሸለም ፡ የርእዮት አለሙን ለሽልማት መታጨት ይህንን ተከትሎ ደግሞ ኢትዮጵያ ውስጥ ስላለው የፕሬስ ሁኔታ የተሰጡ አስተያየቶች በዚህ ሳምንት የኢትዮጵያ ብሎጎች የትኩረት ነጥቦች ነበሩ:: እስክንድር ሽልማቱ ይገባዋል የርእዮት አለሙም ለሽልማት መታጨት አስደስቶናል የሚሉ በርካታ ጽሁፎች ተነበዋል:: ጥቂቶቹን ላቃምሳችሁ:፡ፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማርያም ስለ እስክንድር አንድ ጽሁፍ አሰነብበዋል:: አንድ አንቀጽ እንካችሁ፦

በተረትና በባህላዊ ወጎች በርካታ የተለያዩ ጀግኖች አሉ፡፡አንዳንዶች በሚያጋጥማቸው አደጋ ወቅት በሚያሳዩት የሞራል ጥናካሬ ይጀግናሉ፤አንዳንዶች ደሞ ለክብራቸውን ለዓላማቸውበመቆማቸው ይጀግናሉ፡፡ እንዲሁም አንዳንዶች ጠላቶቻቸውን በፍልሚያው ሜዳ በመግደላቸው ድል በማሸነፋቸው ጀግና ይባላሉ፤ለፍቅር የተሰዉ ጀግኖችም አሉ፤ዘመናዊና ባህላዊ ጀግኖችም ይታያሉ፤ያልታወቀላቸውም ጀግኖች አሉ፤ደግሞም የድል አጥቢያ ጀግኖችም አሉ፡፡ በዚህም ሆነ በዚያ ሁሉም የሚጋሩት አንድ ባህሪ አላቸው፡፡መስዋእትነት፤ታማኝነት፤ጥንካሬ፤ቆራጥነት፤ እርግጠኛነት፤ ያለማወላወል እና ሌሎችም ሁኔታዎች፡፡
ከዚህ ሁሉ በተለየ አካሆን ግን እስክንድር ጀግና ነው! እስክንድር እውነትንና ሃሳቦችን ብቻ በመያዝ የሚዋጋ ጀግና ነው፡፡መነሻው ሃሳብ መድረሻው ሃቅ ነው፡፡ መቀላመድን በእውነት ሰይፍ ያነበረክካል፡፡መሰረተ ቢስና መደለያ ማታለያ የሆኑ ሀሳቦችን በሚቻል፤በሚታመን፤ትክክለኛና ሕዝባዊ በሆነ ሃሳብ ይረታዋል፡፡ብእር ብቻ የጨበጠው እስክንድር ነጋ የሚዋጋው በብእሩ ነው፡፡

ሙሉውን ጽሁፍ ይህችን ጠቅ በማድረግ ያንብቡት:: ስለ ርእዮት ከተጻፉት ደግሞ የአቤ ቶኪቻውን ያዙልኝ አቤ ዜናውም ትንተናውም እንግዲህ በጫወታ መልክ ነው::ከሱም አንድ አንቀጽ ላካፍላችሁ::

በፍትህ ጋዜጣ አምደኛ ሆና በምትሰራበት ወቅት “አሸበርሽ” ተብላ የታሰረችው ርዮት አለሙ “ኢንተርናሽናል ውመን ሚዲያ ፋውንዴሽን” የተባለ ድርጅት የሚዲያ ጀግና ሲል ለሽልማት መረጣት።ሽልማቱ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ራስን ለአደጋ አጋልጦ በጋዜጠኝነታቸው ለተጉ ሴቶች የሚሰጥ ሲሆን፤ ከርዮት አለሙ ጋር አንዲት የፓልስቲን እና አንዲት የአዠርባዣን ጋዜጠኞች ለሽልማቱ ተመርጠዋል።

የአቤ ብሎግ ቢታገድም ብዙ ሀገር ውስጥ የሚታተሙ መጽሄቶች ጽሁፎቹን ያትሟቸዋል:: አቤ ሌላም አንድ ትኩረቴን የሳበ ጽሁፍ አስነብቧል:: ስለሳንሱር ከመጀመሪያው አንቀጽ፦

እኔ የምለው ወዳጄ ሳሱር ነብሴ ድጋሚ መጣች አይደል እንዴ!? እሰይ! እልል በሉ እንጂ። ድግስ አትደግሱም እንዴ!? ጠላው ይጠመቅ፣ ድፎው ይደፋ፣ ቡናውም ይፈላ፣ ፈንዲሻው ይፈንደሽ፣ እጣን ሰንደሉ ተጫጭሶ ቄጤማውም ይጎዝጎዝ። በዓሉ የትንሳኤ በዓል ነውና ሁሉም ሰው ይደሰት።

አቤ ባሽሙር ተደሰቱ ቢለንም ይሄ እንግዲህ ብሎጎችን ከማገድ ያልተናነሰ ህግን የሚጥስ ነው:: የሀገሪቱ የአየር ሞገድ በአንድ እይነት ድምጽ ብቻ መሞላቱ በርግጥ አሳሳቢ ችግር ነው:: ወደ ተስፋዬ አለማየሁ አለፍኩ በሁለት ሃገራት ያሉ የሚመስሉ የመገናኛ ብዙሃን− የግል እና መንግስት ጋዜጠኝነት ሲፈትሽ በሚል ርእስ ኢትዮጵያ ውስጥ ልማታዊ ጋዜጠኝነት አለ ብለው ለሚከራከሩ ወገኖች መልስ የሚሆን በግል እና በመንግስት የመገናኛ ብዙሃን ላይ ታትመው የወጡ ዜናዎችን በመሰብሰብ አጠር ያለ ይዘታዊ ትንተና ሰርቶ ግንዛቤ የሚያስጨብት ጽሁፍ አስነብቧል:: እንደ ማጓጓያ አንድ አንቀጽ ላቅርብ:

እስቲ ጥቂት ስለ ጋዜጠኝነት አላባውያን እናውጋ እና ከዚያ ወደ ተነሳሁበት ሃሳብ አንድ ሁለት እያልን አብረን እንዘልቃለን፡፡ ከጋዜጠኝነት አላባዎች ቀዳሚዎቹ እና ዋነኞቹ ነፃ ትክክለኛ እና ሚዛናዊ መረጃን ለህዝብ ማድረስ ናቸው፡፡ ይህን ለማድረግ ደግሞ ለህዝብ ታማኝ በመሆን ለእውነት ዘብ መቆም ከአንድ ጋዜጠኛ ከሚጠበቁበት መሰረታዊ ግዴታዎች ውስጥ ዋነኞቹ ናቸው፡፡ ለእውነት ዘብ መቆም እና ለህዝበ ታማኝ መሆን፡፡ እነዚህ ሁለት ነጥቦች በዋነኛነት ላተኩር የፈልግኩባቸው ነጥቦቼ እንጂ ሌሎቹን ዘንግቼ አይደለም፡፡ ለእውነት ዘብ መቆምን እና ለህዝብ መታመንን ይዘን አብረን እንዘልቃለን፡፡ እነዚህን ሁለት ነገሮችን በዋነኛነት ያልቋጠረ ጋዜጠኛ ለሌሎቹ ግድ ላይኖረው ይችላል፡፡ ሁለቱን በመሰረታዊነቱ ከያዝን በኋላ ግን ልማትን ጨምረን በሃገራችን ያለውን የጋዜጠኝነት ትግበራ እንፈትሸዋለን፡፡ ልማት ስንጨምርበት ደግሞ ለአንድ ማህበረሰብ የጋዜጠኝነት እና የጋዜጠኛው ሃላፊነት እና አስፈላጊነት በጣም ከፍ ይላል፡፡ ሃላፊነትን የሚሸከም ደንደን ያለ ትከሻ እና ብርቱ ጉልበት ይልጋል፡፡ ጋዜጠኝነት ከባድ ሃላፊነት ነው፡፡ በተለይ ደግሞ ልማታዊ ጋዜጠኝነት፡፡

ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ጠቅ ያድርጉ::

ከተስፋዬ የመገናኛ ብዙሃን የዘገባ ሽፋን ይዘታዊ ትንተና ጋር በቀጥታ ግንኙነት ስላለው ርዕሰ ጉዳይ ልለፍ:፡ ላለፉት አስራ አንድ እና አስራ ሁለት ሳምንታት በኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች እና በእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ወይም መጅሊስ መካከል የነበረው አለመግባባት እየተካረረ በመምጣቱ መንግሥት ሐሙስ ዕለት ባወጣው መግለጫ ሃይማኖትን ሽፋን በማድረግ ሁከት ለመፍጠር እየሞከሩ ናቸው ለሚላቸው ወገኖች ሕገመንግሥታዊ ሥርዓቱን እንዲያከብሩ ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል :: መግለጫው እስከሚሰጥበት እለት ድረስ ቀን የመንግስት የመገናኛ ብዙሃን ስለተፈጠረው አለመግባባት እና በአወልያ ትምህርት ቤት እና በታላቁ አንዋር መስጊድ ዘውትር አርብ ለሶስት ወራት ገደማ ሲካሄድ ስለነበረው የተቃውሞ መግለጫ ብዙም አልዘገቡም ነበር:: መግለጫውን ተከትሎ ብሎጎች እና የማህበራዊ ድረገጽ ተጠቃሚዎች ግን የትኩረት ነጥባቸው አርገውት ነበር:: ኢትዮ አንድነት የተሰኝ ብሎግ ይህንን ጉዳይ በማስመልከት ሁለት የሌሎች ሚዲያ ዘገቦችን አስነብቧል። እዚህ እና እዚህ ላይ ጠቅ ቢያደርጉ ያገኟዋቸዋል::

አቤል በዚህ ሳምንት በቅርቡ 82ኛ የልደት በአላቸውን ስላከበሩት ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማሪያም አስነብቦናል:: ኢትዮጵያዊው ጆርጅ ኦርዌል ይላቸዋል:: እስቲ አንድ አንቀጽ፦

መቼም ‘Animal farm’ን የሚተካከል ተሳልቆ (ሳታየር) አላነበብንም፡፡የዚህ መጽሐፍ ደራሲ የብዕር ስሙ ጆርጅ ኦርዌል ሲሆን ትክክለኛ ስሙ ኤሪክ ብሌር ይሰኛል፡፡ዛሬ ስሙን ላነሳሳው የፈለኩት ያን ጋዜጠኛ፣ መምህር ፣ ወታደር እና የተባ ብዕረኛ ሳይሆን ኢትየጵያዊውን ጆርጅ ኦርዌል ነው ፡፡ ይህ ኢትዮጵያዊ መምህር ፣የካርታ እና ጂኦግራፊ ባለሙያ ፣ የዕድሜ ልክ ሐያሲ ፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ፣ በምክንያት ፓለቲከኛ ሲሆን የኛን እንስሳት ዓለም ለማሳየት እንደጆርጅ ኦርዌል ልብወለድ መጻፍ አላስፈለገውም፡፡ ለብዙ አመታት ስለ ሕገ አራዊትና ሕገ ሐልዮት በግልጽ እየተነተነ አሳየን እንጂ፡፡ ሰው እንድንሆን መሞገት ከጀመረ እንደሰነበተ የምንረዳው ከሁለት አገዛዞች በፊት በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት በተደረገ የዕድሮች ስብሰባ ያደረገውን ንግግር ስናነብ ነው፡፡

ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ጠቅ ያድርጉ::

በነገራችሁ ላይ ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማሪያም በስማቸው የተሰየሙ ብሎጎች አላቸው:: አንዱ ቆየት ያለ እና ፕሮፌሰር መስፍን ለተለያዮ መገናኛ ብዙሃን የሰጡትን ቃለምልልስ እና አንድ አንድ ስራዎቻቸውን የያዘ ነው እዚህ ላይ ጠቅ ቢያደርጉ ያገኙታል:: ሁለተኛው ውቅታዊ ጽሁፎችን የሚያስነብብ ብሎግ ነው:: በዚህ ሳምንት አንድ በፍትህ ጋዜጣ ላይ የታተመችን የመንግሥት ሌቦች አደራ-ቢስነትና ሕዝብ ኃላፊነት በሚል ርእስ የተጻፈች ጽሁፍ በድጋሜ አስነብበዋል:: ይችን ጠቅ በማድረግ ያንብቡት:: ፍትህ ጋዜጣን ለማታገኙ እስቲ አንድ አንቀጽ፦

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተደጋጋሚ ስለመንግሥት ሌቦች እየተናገረ ነው፤ ሌቦቹን ግን እሱም አያውቃቸው፤ እነሱም እየሰሙት አይደለም፤ የመንግስት ሌቦች የተባሉት የሚግጡባቸው ዋናዎቹ መስኮች ታክስ፣ መሬትና የንግድ ውድድር መሆናቸውንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጾአል፤ ከዚህም በላይ የተባሉትን የሌብነት መስኮች ከለምነት ወደበረሃነት ለመለወጥ የኢትዮጵያ ህዝብ ኃላፊነት አለበት ያለ መሰለኝ፤ ሥልጣን ሳይኖር ኃላፊነት ከየት ይመጣል? እንግዲህ የፌዴራል ፖሊሱንና ሌላውን አልፎ፣ የደኅንነቱን ሰራዊት አልፎ፣ የጸረ-ሙስና ኮሚሽንን አልፎ፣ ዓቃቤ ሕግን አልፎ ሕዝብ እነዚያን ለምለም መስኮች ማድረቅ እንዴት ይችላል? ሌቦቹ ያሉት በመንግስት ጎራ ብቻ ሳይሆን በህዝብም ጎራ እንደሆነ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠቆም አድርጎአል፤ እንዲህ ከሆነ ‹‹አባቱ ዳኛ ልጁ ቀማኛ›› የሚባለው ሁኔታ ሰፍኖአል ማለት ይመስላል፤ ይህ እውነት ከሆነ ሌብነት ሥርዓት ሆኖአል ማለት ነው።

በፍቄ በዚህ ሳምንት ስለአብዮት አስነብቦናል:: አብዮት ምን እንደሆነ እና ኢትዮጵያ ውስጥ ስላለው ነባራዊ ሁናቴ ጋር በማዛመድ አንድ ብሏል:: አንድ አንቀጽ፦

አብዮት – ከዚህ ቀደም እንዳወራነው – የእንግሊዝኛውን Revolution እንዲተካ ‹‹በደርግ›› የተመረጠ፣ የግዕዙን ቃል ‹አበየ› (Revolut) መሠረት አድርጎ የተሰየመ ቃል ነው፡፡ አብዮት – መንግሰትን ወይም ርዕዮተ ዓለምን የመተካት ሒደት ነው፤ አብዮት – ድንገታዊ እና ፈጣን ክስተት ነው፡፡

ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ ትይይዙ ላይ ጠቅ ቢያደርጉ ይከፍትሎታል::

በመጨረሻም አሁን አሁን ስነ:ጽሁፋዊ ብሎጎች እየተበራከቱ ናቸው:: ዛሬ አንድ ጀባ ልበላችሁ እና የብሎግ ክለሳዬን ላብቃ :: ቤዋዬ ይባላል የብሎጉ ስም ሙሉ በሙሉ ለስነጽሁፍ የተከፈተ ብሎግ ነው:: በዝህ ሳምንት አጭር ልቦለድ አሰነብቦናል:: መሳጭ ቋንቋው እና አዝናኝ አተራረኩ ደስ ይላል:: ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ ትይይዙ ላይ ጠቅ ቢያደርጉ ይከፍትሎታል:: መልካም ሳምንት::

የኢትዮጵያ ብሎጎች ምን ጻፉ?

የአሁኑን ሳምንት የኢትዮጵያ ብሎጎች ክለሳ ስሰራ ትልቁ ተግዳሮቴ የነበረው አብዛኞቹ ካሁን በፊት በዘዴ ወኪል ሰርቨርን በመጠቀም የማነባቸው ብሎጎች አብዛኞቹ ወኪል ሰርቨሮችም ጭምር ስለታገዱ እስከ ቅዳሜ ጠዋት ድረስ ማንበብ አልቻልኩም ነበር:: ሳይደግስ አይጣላም እንዲሉ በወኪል ሰርቨሮች በኩል ማንበብ ያቃተኝን ጽሁፍ ከሀገር ውጪ ያሉ ወዳጆቼ እንዳለ ገልብጠው በውስጥ የኢሜል አድራሻዬ በኩል እንደ ቅጥያ ዶክመንት ልከውልኝ ማንበብ ችያለሁ:: ሌሎች ያልታገዱ አዳዲስ ወኪል ሰርቨሮችንም እንድሞክራቸው ልከውልኝ መጠቀም ችያለሁ:: ስላጋጠመኝ ችግር እና የሳምንቱ አብይ ጉዳይ ሆኖ የብዙ ብሎግ ጻሀፊያንን ትኩረት ስቦ ስለነበረው የብሎጎች እገዳ ይህችን ታህል ካልኩ ሌሎች ምን እንዳሉ እስቲ ላቃምሳችሁ:: በፍቄን ላስቀድም በፌስቡክ ግድግዳው ላይ አጭር ጽሁፍ አስነብቦ በብሎጉ ላይ ኢትዮጵያ መንግስት መጠላቱን የሚያሳብቁ ምልክቶች በሚል ርእስ የጻፈውን ጽሁፍ ትይይዝ አስቀምጧል:: ሙሉውን ጽሁፍ ትይይዙን ጠቅ በማድረግ ይከፈቱት አልከፍት ካሎት በፍቄ በፌስቡክ ግድግዳው ላይ ያሰቀመጠውን ጽሁፍ በማንበብ ይሞክሩት:

“መንግስት ለምን ትንንሾቹን – ሰላማዊዎቹን ሰዎች ለማጥቃት በርካታ ገንዘብ እና ጊዜ እንደሚያባክን አልገባኝም:: ዛሬ የጻፍኩትን ጽሁፍ እኔ ራሴ ማንበብ እንዳልችል ሆኖ ታግዷል:: የሚገርመው በጽሁፉ ውስጥ ሐሳብን በነፃ ስለመግለጽ መብት የተናገርኩት ነገር ነበር:: በፕሮክሲ በመታገዝ ለመክፈት ስታገል ጉግል ራሱ .com የነበረውን .ca በማድረግ ያለፕሮክሲ እንድከፍተው ታድጎኛል:: ያው እናንተም ይህንኑ ተከተሉ:”

ብሎግ ማገድ ፈጽሞ የማይቻል ነገር እየሆነ መምጣቱን ቻይናውያንም ጠንቅቀው ያውቁታል:: ለነገሩ ቻይናውያን እንኳ ሲያግዱ አይናቸውን አፍጠጥው አላገድንም አይሉም ድድ ላይ የማይላከክ ምክኒያት እንኳ በትንሹም ቢሆን ይሰጣሉ እንጂ::
ወደ አቤ አለፍኩኝ በዚህ ሳምንት ከማሸሟጠጥ በተጨማሪም ብሎግ መክፈትም ስራዬ ሆኗል ብሎ በፌስቡክ ግድግዳው ላይ የጻፈው አቤ :ለ7ኛ ግዜ ብሎግ ከፍቷል:: አቤ ድብብቆሽ የሚጫወት እስኪመስል ድረስ በዚህ መጣሁ በዚህ ሾለኩ እያለ ብሎግ ሲከፍት እጁ የነካውን ሁሉ ማግድ በውነት ትዝብት ላይ የሚጥል ነው:: ይሄ ልጅ ምን ቢጽፍ ነው እንዲህ እጅ እጁን እየተከተሉ የሚዘጉት ለምትሉ ለ7ኛ ግዜ በከፈተው ብሎጉ የአንጋፋው ደራሲ ስብሐት ገብረ እግዚአብሄርን አንድ ጨዋታ ጨምሮ በርካታ በርካታ ጨዋታዎችን አስነባቧል:: ካልታገደ ትይይዙን ጠቅ በማድረግ ይሞክሩት:: መንግስት በእውነት የግለሰቦችን ብሎግ እየተከታተለ ይዘጋልን? እኔ ግን መንግስት እንዲህ ያለውን ነገር ይፈጽማል ብይ ማመን ይከብደኛል:: ይህ ጉዳይ ሰፊ እና ለብቻው ሰፊ ዘገባ የሚሻ ስለሆነ ወደ ብሎግ ምልከታዬ ልመለስ::

ቀጠልኩ እግር ኳስ የምትከታተሉ ሰዎች ያለፈውን ሳምንት የምታስታውሱበት በርካታ ነገሮች ተከስተው ነበር:: የባርሴሎና ከአውሮፓ ቻምዮኖስ ሊግ መወገድ ግን አንዱ እና ዋንኛው ነው:: ይህንን ጨዋታ ዳንኤል ክብረት የነብሴ ጨዋታ ይለዋል:: ለምን ይሆን የነብሴ ጨዋታ ያለው እስቲ አንድ አንቀጽ እንደ ማጓጓያ:

ከጨዋታው በፊት ባርሴሎና ቼልሲን በኑካምብ ሜዳ ላይ ድባቅ ሊመታው እንደሚችል የሚተነብዩነበሩ፡ ቼልሲ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ያለውን ቦታና ሰሞኑን ያስመዘገባቸውን ደካማ ውጤቶችተንተርሰውባርሴሎና ያሰለፋቸውን ምርጥ ተጨዋቾች ቆጥረው፣ የአሰልጣኝ ጋርዴዎላን ብቃትአሞካሽተው ለቼልሲ የፈሩለት ብዙዎች ነበሩ፡፡ ምንም እንኳን በስታምፎርድ ብሪጅ ቼልሲበድሮግባ ጎል ባርሴሎናን አንድ ለባዶ ቢያሸንፍም፤ያ ግን አጋጣሚን እንጂ የቼልሲን ብቃት፣የባርሴሎናንም መውረድ እንደማያሳይ የተከራከሩ ነበሩ፡፡ «ደርሶ አይቼው» አለ አማራ ለልጁ ስም ሲያወጣ፡ ትናንት ደረሰና ሁሉንም አየነው፡፡ የተጠበቀውቀርቶ ያልተጠበቀው ሆነ እኔም ከጨዋታው በኋላ ነፍሴን እንዲህ አልኳት፡፡ ነፍሴ ሆይ በርቺ፡፡ ተስፋም አትቁረጭ ምናልባት ከፊትሽ የምትጋጠሚው ፈተና በዓለም ላይ ወደርየሌለውና ለማሸነፍ ከባድ መስሎ የሚታይ ይሆን ይሆናል፡፡ ምናልባትም ብዙዎቹን የረፈረፈ፤ ታላቅስምም ያተረፈ ይሆን ይሆናል፡ ምናልባትም ደግሞ የዓለም ሻምፒዮናነትን ክብር የተቀዳጀ ታላላቅየተባሉትን ሁሉ ድል እየመታ የመጣም ሊሆን ይችላል፡፡ ግን ነፍሴ ሆይ በርቺ፡

ዳንኤል ክብረት በሳምንቱ ይህንና ሌሎች ጽሁፎችንም አስነብቧል:: እዚህ ላይ ጠቅ በማድረግ ያንብቡት::

ስነጽሁፍ በተለይ ግጥም የምትወዱ ከሆናችሁ በዚህ ሳምንት ብሎጎች በርካታ ግጥሞች አስነብበውናል:: ተስፋዬ ገ/አብ መራር ስነግጥሞች በሚል ርእስ የበርካታ እውቅ ገጣሚያንን ግጥሞች አስነብቧል:: ከመንግስቱ ለማ ቀንጨብ ያደረገውን ላካፍላችሁ::

ባልን ቢያስተያዩት – ከሚስቲቱ ጋራ፣
እሷ አፍለኛ ሆነች – ያ! ሻጋታ እንጀራ፣

በሌሎቹ ስነግጥሞች ለመደሰት ትይይዙን ጠቅ ያድርጉት:: ታዲያ ካልከፈተ ከላይ የበፍቄን ምክር አይዘንጉ:: ለሌሎችም ብሎግ ስፖት (blogspot)ላይ የሚገኙ ብሎጎችን ለመክፈት ይጠቀሟቸው:: ከስነግጥም ብሎጎች ሳንወጣ አደም ሁሴን ናፍቆቴን ነጠቁኝ የሚል ግጥም አስነብቦናል:: እዚህ ላይ ጠቅ በማድረግ ዘና ይበሉበት::

በዚህ ሳምንት ተስፋዬ አለማየሁ ስለ ኢትዮጵያዊ መፈክሮች ስለታሪካዊ አመጣጣቸው እና ስለ ተጽእኗቸው አስነብቦናል:: እንደ ማጓጓያ አንድ አንቀጽ ላካፍላችሁ:: ቀሪውን እናንተ ትይይዙን ጠቅ በማድረግ ያንብቡት::

ህብረተሰባዊት ኢትዮጵያን መሰርተው አንድ ቋንቋ ተናግረው፣ አንድ ጥይት ተኩሰው፣ አንድ አቢዮት አፈንድተው፣ አንድ ትውልድ ፈጅተው፤ በጡጫ እና በግልምጫ ልቀው ከወጡት የወቅቱ መሪ ስም ጋር. . .ወደፊት፣ “ሁሉም ነገር ወደ ጦር ግንባር” እያሉ ይፎክሩ ነበር፡፡ በየመድረኩ በሚደረጉ ህዝባዊ ስበሰባዎችና ንግግሮች ላይም “እናት ሃገር ኢትዮጵያ ወይም ሞት” ፣”ህብረሰባዊነት ይለምልም”፣ “. . . ለኢምፔሪያሊስቶች “

አካባቢ የተባለ ብሎግ ስለ ጾም እና አካባቢ ትይይዝ መሳጭ በሆነ ቋንቋ አስነብቦናል:: እዚህ ላይ ጠቅ በማድረግ ግንዛቤዎትን ያዳብሩበት::

ክረምት ላይ ኢትዮጵያውያን በጉጉት የሚጠብቁት የለንደን ኦሎምፒክ ይካሄዳል:: በዳጉ የአለም አትሌቲክስ ሻምዮና ኢትዮጵያ ያስመዘገበችው ውጤት ደካማ ስለነበረ በለንደን ውጤታችን ምን ይሁን ብለው የሚጠይቁ ኢትዮጵያውያን ብዙ ናቸው:: ስለዚህ በወንዶች ማራቶን ኢትዮጵያን በለንደን ኦሎምፒክ እነማን ይወክሏታል? የሚለውን የፍሰሀ ተገኝን ጽሁፍ ማንበብ ደግሞ በዳጉ የአለም አትሌቲክስ ሻምዮና የተመዘገበው ደካማ ውጤት እንዳይደገም በወንዶች ማራቶን ኢትዮጵያን የሚወክሉትን አትሌቶች በጥንቃቄ እና በርካታ መስፈርቶችን ከግምት ውስጥ ያስገባ መረጣ እንዲደረግ ያስገነዝባል:: አንድ አንቀጽ እንካችሁ:

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንም በምርጫው ላይ ከአመታዊ ፈጣን ሰአቶች በተጨማሪ እንደ ጸጋዬ ከበደ ያሉ በታላላቅ የአለም አቀፍ ውድድሮች ላይ የአሸናፊነት ልምድ ያላቸው አትሌቶችን ለለንደኑ ኦሎምፒክ ማካተት አለበት። በአለፈው እሁድ ለንደን ላይ በተካሄደው የማራቶን ውድድር ሶስተኛ የወጣው ጸጋዬ፤ በ2009 ዓ.ም የለንደን ማራቶን አሸናፊ፣ በቤጂንግ ኦሎምፒክ የነሀስ ሜዳሊያ ባለቤትና በበርሊኑ የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የነሀስ ሜዳሊያ ባለቤት ነው። የጸጋዬ ከበደ ጠንካራ ጎን ብቃቱ የማይዋዥቅ መሆኑና በአብዛኛው ፈጣን የሚባሉ ሰአቶቹን ያስመዘገበው አስቸጋሪና ፈታኝ እንደሆኑ በሚነገርላቸው ለንደን፣ ኒው ዮርክ እና ቺካጎ ከተሞች ውስጥ በተካሄዱ የማራቶን ውድድሮች ላይ ነው። የሚገርመው በእነዚህ አስቸጋሪ የማራቶን መወዳደሪያ ስፍራዎች ቢሮጥም ያስመዘገባቸው ሰአቶች በአማካይ 2 ሰአት ከ06 ደቂቃዎች መሆናቸው ነው።

ፍስሀ ሌላም ማራኪ ጽሁፍ አስነብቦናል ስለ ባርሴሎናው ድንቅ ልጅ ፔፕ ጋርድዮላ:: ፔፕ ከባርሴሎና አሰልጣኝነት አራት ድንቅ የውድድር አመቶች ካሳለፈ በኋላ እንደማይቀጥል ይፋ በማድረጉ በርካታ የአለም መገናኛ ብዙሀን ሰፊ ሽፋን ሰጥተውታል::ስለዚህ ድንቅ እና ትሁት ካታሎናዊ ለኢትዮጵያውን በሚመች የአተራረክ ዘይቤ ቀርቧል:: እዚህ ላይ ጠቅ በማድረግ ይዝናኑበት::

Why Eskinder deserved the Barbara Goldsmith Freedom Pen Award?

Considering his toil for freedom of expression, it might not be surprising to hear that Eskinder Nega won PEN/Barbara Goldsmith Freedom award. Besides, Pen international have had enough reasons to honor him, but I think that shouldn’t stop you from hearing my reasons why Eskinder Nega deserved the Barbara Goldsmith Freedom I’ll try my best to explain why.
Let me start with my own plight in writing this piece; online and offline friends have been continuously warning me not write about Eskinder for one thing he is now faces terrorism charges, and if convicted the same charge will turn against me as most journalists were accused of using journalism profession to support terrorism; for another, there is a high risk of being labeled as an enemy of state by sycophantic members of the ruling party.
People who intimately track even the smallest amount of retreat or progress of Ethiopian journalism in a rugged Ethiopia’s media landscape might be well aware of the fact that Ethiopian journalists are usually divided along with major journalistic contours of views as pro-government and critical journalists. Some say Ethiopia’s journalism is in the state of brink as government’s tough fists over press have ever been increasing since the contentious election of 2005. Others argue government has changed the spotlight of the press to more positive governmental ventures with the China’s technical help. Recently Mohamed Keita in his article on New York Times highlights that China has been deepening technical and media ties with African governments (Ethiopian) to counter the kind of critical press coverage that both parties demonize as neocolonialist [sic]. Still others say that there is a phantom of critical journalism in Ethiopia with the help of few fearless journalists who are loyal to accuracy, independence, fairness, transparency – core values of journalism. For me it is graceful to pick Eskinder Nega as one of those who are working in gloomy and ever thinning critical journalistic conventions of Ethiopia. In fact Eskinder is not the only gem of tattered Ethiopian modern day journalism, my favorite stalwarts of Addis Neger journalists, Dawit Kebede, Wubeshet Taye and of course Reyot Alemu are all creditable for their daring attempt in becoming alternative voices in Ethiopian media landscape. But Eskinder is a highly remarkable emblem for freedom of expression. In a time when many journalists not succeeded in enduring horrendous pressures from a range of interest groups, both financially and politically, Eskinder was something of a matchless: a well-behaved and top end professional who did not succumb to either exile and or silence.
Eskinder who started his ply in Ethiopian journalism with his first newspaper, Ethiopis, was among the first newspapers of the then flourishing Ethiopia’s independent media. Then followed by Asqual, Satenaw, and Menelik unfortunately all of them shut down by authorities. Then he has turned to be a columnist for varies media. This signals he has done everything possible the country’s political system has offered for critical journalists like him.
I used to read Eskinder’s journalistic and opinion pieces before his incarceration with enthusiasm. Most of his works are great journalistic piece of work. Despite a number of barriers to disconnect Eskinder from public, his works are still available thanks to social media and his own effort. His English and Amharic works are well-written and authoritative. Eskinder’s journalistic career illustrates a predicament of all Ethiopia’s critical voices that is situated in the political, social and economic context in which I myself experiencing. Eskinder’s case presents how inequitable Ethiopia’s media is and how things such as freedom of thought that are taken for granted even in our neighbor Kenya is isolated unjustly from Ethiopia. His career is filled with allegations, incarcerations and intimidations and all because of foibles and frailties of government. Eskinder is extremely passionate for freedom of expression and other human rights justice—a man who gave his life to the cause of justice. There is no a reservation or whatsoever that his life makes a significant contribution to Ethiopian journalism.

ከሚያዚያ 06 እስከ ሚያዚያ 13 የኢትዮጵያ ብሎጎች ምን ጻፉ?

በዚህ ሳምንት የሀገር ቤት የህትምት ውጤቶችም ቢሆኑ የማህበራዊ ደረ፡ገጾች እና ብሎጎች በስፋት ሲያንሱ ሲጥሉ የነበሩት ቴዲ አፍሮን እና እጮኛው አመለሰትን ነበር:፡ ቴዲ አዲስ አልበም ስላወጣ እና የእጮኛውን ማንነት በራዲዮ ቃለ ምልልስ ወቅት ይፋ ስላደረገ ያገኝው ሽፋን ይመስለኛል:: ለነገሩ አቤ ቶክቻው ይህንን በማስመልከት የቴዲ ሰሞን ገባ ብሎ አልበሙን በማስመልከት ባለፈው ሳምንት አልበሙን በማድነቅ በተለይ የአልበሙ መጠሪያ የሆነውን ጥቁር ሰው የሚለውን ዘፈን ምንሊክን ዳግም ያነገሰ ብሎ ከትቦ ነበር:: አልበሙ ከመውጣቱ በፊትም ማርቆስ በእንግሊዝኛ የቴዲን አልበም ልገዛ የምገደድባቸው አምስት ምክኒያቶች ብሎ ጽፎ ነበር :: ዘላለም ማልኮም ክብረትም ጥቁር ሰው የሚለው ዘፈን የኢትዮጵያን ታሪክ ባጭሩ የሚያስተምር ነው ይለዋል:: ነገር ግን በፍቃዱ ዘሃይሉ የቴዲን አልበም የጠበቀውን ያህል ጥሩ አለመሆኑን ገልጾ አልበሙን ያልገዛባቸውን አምስት ምክኒያቶች ዘርዝሮ ጽፏል:: ዲ ብራሀን ደግሞ ተነባቢነት ያገኝ ሰፊ ዘገባ ይዞ ወጥቷል:: ሁሉንም አንብቧቸው የሰሞኑን ወሬ ጭብጥ በሚገባ ያስቃኞታል: ግንዛቤዎ ሙሉ እንዲሆን: ታዲያ የፎርቹንን እና የአድማስን የፊት ገጽ ዘገባ እንዳይረሱ:: የፎርቹን ድረ ገጽ ምናልባት ባይከፍትሎት ሸገር ትሪቡን ላይ ያገኙታል::

ቴዲ እና አልበሙ አነጋጋሪ ቢሆኑም ሌሎችም አበይት ጉዳዮች ነበሩ ምንም እንኳ የማህበራዊ ደረ፡ገጽ ተጠቃሚዎች እና ብሎጎች ለቴዲ የሰጡትን ትኩረት ባይሰጧቸውም ዋና ዋናዎቹን እስቲ እንያቸው:: ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ ለተወካዮች ምክር ቤት በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ በሰጡት ማብራራያ የተነሳ ከተጻፉት ብሎጎች ልጀምር:: አቤ ቶክቻውን እናገኛለን: አቤ እንዲህ ይላል፤ ጠቅላይ ሚኒስተሩ ስለመምህራኑ ማብራሪያ ተጠይቀው ማረሪያ ሰጡ!:: ሙሉውን ዜና ለማንበብ እዚህ ላይ ጠቅ ያድርጉ::

ኤፍሬም ኤሼቴ አደባባይ በሚሰኝው ብሎጉ “ጠ/ሚኒስትሩ ስለ ማኅበረ ቅዱሳን በተናገሩት አልስማማም” የሚል ጽሁፍ አስነብቧል:: ከመጀመሪያው አንቀጽ፤

ማክሰኞ ሚያዚያ 9/2004 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ለምክር ቤቱ ሪፖርት ካቀረቡ በኋላ እንደተለመደው የምክር ቤቱ ክቡራን አባላት በንባብ ላቀረቡላቸው ጥያቄዎቻቸው መልስ ሲሰጡ ተከታትያለኹ። ከጥያቄዎቹ አንዱ ወቅታዊው የሙስሊሞች ጉዳይ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምላሻቸው “መንግሥት በሃይማኖት ውስጥ ጣልቃ አልገባም” የሚለውን በሰፊው ሲያብራሩ ቆዩ። አንዱ ማብራሪያቸው ስለ ሰላፊያዎች (አል-ሰላፊያ ወይም ወሐቢያዎች) ነው። ራሳቸውን “አል-ሰላፊዩን” የሚሉትና ትክክለኛውን የቁርዓን ትምህርት እንከተላለን የሚሉት የሙስሊም ክፍል የሆኑትና መሠረታቸውን በሳዑዲት አረቢያ ያደረጉት ጽንፈኛ ወገኖች በተቃዋሚዎቻቸው ደግሞ “ወሐቢያዎች” ይባላሉ። የዚህ ጽሑፍ ዓላማ ስለ ወሐቢያዎች እና ስለአክራሪነታቸው ማተት ስላልሆነ የዚህን ቡድን አስተምህሮ እና በኢትዮጵያ ላይ ስለ ጋረጠው ከፍ ያለ አደጋ “አክራሪ እስልምና በኢትዮጵያ” (ኤፍሬም እሸቴ፣ በ2000 ዓ.ም/ 2008 የታተመ) የሚለውን መጽሐፍ ማንበብ እንደሚቻል በመጠቆም አልፋለኹ።

ሙሉ ጽሁፉን ለማንበብ እዚህ ላይ ጠቅ ያድርጉ::

የሙስሊም ጉዳይ መጽሄት ሲኒየር ኤዲተር አክመል ነጋሽም የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ንግግር በተመለከተ በፍትህ ጋዜጣ ላይ የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ዲስኩር ግዝፍት እና ግድፈት በሚል ጽሁፍ የራሱን አስተያየት ሰጥቷል:: ደረ ገጽ ላይ ላገኝው ባለመቻሌ እዚህ ላይ ትይይዙን ማኖር አልቻልኩም:: አርብ ሚያዚያ 12 2004 ከታተመችው ፍትህ ላይ ገጽ 12 ላይ ሊያገኟት ይችላሉ::

በዚህ ሳምንት ፌስቡክ እንደሌሎች ሀገሮች ሁሉ በኢትዮጵያም ለቁምነገር ሊውል እንደሚችል የታየበት አጋጣሚ አዲስ አበባ ላይ ታይቶ ነበር:: የአለም ደቻሳን ቤተሰቦች ለመርዳት እትዮጵያውያን በፌስቡክ ከያሉበት ተጠራርተው በዋቢሸበሌ ሆቴል የስነጽሁፍ ዝግጅት አድርገዋል:: የዚህ ስብስብ ስም ደጉ ኢትዮጵያዊ ይሰኛል:: በዚህም ሃያ ሺህ የኢትዮጵያ ብር ከትኬት ሽያጭ እንደተገኝም በግሩፑ የፌስቡክ ገጽ ላይ ሪፖርት ተደርጓል :: ስለዚህ መልካም ተግባር ሪፖርተርም ከልብ ካለቀሱ እምባ እንደማይገድ ያስመሰከረ ስብስብ … በማለት በድረ ገጹ ዘግቧል:: በነገራችሁ ላይ የዚህ ግሩፕ ቁጥር አባላት 4000 በላይ ሆኗል እና አሁንም እያደገ ነው:: በተጨማሪም በዚህ መልካም ተግባር በርካታ ብሎግ ጻሃፊዎች እና የግሩፑ አባላት ደስታቸውን በግሩፑ የፌስቡክ ገጽ ገልጻዋል::

የኢትዮጵያ ብሎጎች እለት እለት እየጨመሩ ነው:: ነባር ጽሃፍትም የራሳቸውን ብሎግ እየጀመሩ ነው :: ዛሬ አንድ ሁለት ላስተዋውቃችሁ ። ከአደም ሁሴን ልጀምር አደም ሁሴን የአለም ደቻሳን ቤተሰቦች ለመርዳት በተዘጋጀው የገቢ ማሰባሰቢያ የስነጽሁፍ ዝግጅት ላይ ተግኝቶ የተሰማውን ስሜት በፌስ ቡክ ገጹ ላይ ገልጻል:: ግጥሙ የዝግጅቱ ለት የተገጠመ ባይሆንም ለዛ ያለው ግጥም እና መጣጥፍ በብሎጉ ላይ ብቻዩን አይደለሁም በሚል ርእስ አትሞ አሰነብቦናል :: እዚህ ጋር ጠቅ በማድረግ ተጋበዙልኝ ::

ሌላው ተስፋዬ አለማየሁ ነው:: እንደ አደም ሁሉ ተስፋዪም በሁለት የስነፅሁፍ ዘውጎች ፡ በግጥም እና በመጣጥፍ ብሎግ ከጀመረ አንድ አመት ሆኖታል:: በዚህ ሳምንት በበዕል አሳበው የዋጋ ቅናሽ አድርገናል እያሉ ገዢ ትርፍ የሚያጋብሱ ነጋዴዎችን የታዘበበትን ጽሁፉን “ቢግ ዲስካውንት. . . ወይስ ሜኪንግ ቢግ አካውንት ?” በሚል ርእስ አስነብቦናል:: እዚህ ጋር ጠቅ በማድረግ ዘና ይበሉበት::

ተስፋዬ ገ/አብ በዚህ ሳምንት ሁለት ጽሁፎች አስነብቦናል:: የጎጃም ልዕልት እና ጎሹም ሄደላችሁ የሚሉ:: የጎጃም ልዕልት ከምትለዋ አስቲ አንድ አንቀጽ እንካችሁ::

“የእናቷን ውበት ወርሳለች” ይሏታል። ርግጥ ነው፣ ወይዘሮ ላቀች ይህ ቀረሽ የማይባሉ ደርባባ ወይዘሮነበሩ። የቀድሞ የወጣትነት ወዘናቸው ወደ ልጃቸው ተሻግሮ ማየት ችለዋል። በዚህም ተባለ በዚያ ልጅቱየንጉስ ተክለሃይማኖት ሴት ልጅ ናት። ስምን መልአክ ያወጣዋልና ስሟ ንግስት ይባላል። ስለዚህ ቆንጆ ናት።ከቁንጅናዋ በላይ ግን ሊጠቀስላት የሚችል ቁምነገር ነበራት። ከደብረ ኤልያስ ገዳም በመጡ ሊቃውንትፅህፈትና ቅኔ ተምራ ነበር። አባቷ እያሉ አጊጣለች። ርግጥ አሁን ፀሃይ ጠልቃባት ነበር…

ሙሉውን ጽሁፍ ትይይዙን ጠቅ በማድረግ ዘና ያንብቡት::

አሁን ሱስ ወደሲያዘኝ የፍሰሀ ተገኝ ብሎግ ልውሰዳችሁ:: ፍሰሀ ዛሬ ደግሞ የሀገራችንን የእግር ኳስ መሰረታዊ ችግር ገራ ገር በሆነ ቋንቋ አሰነብቧል:: ደግሜ ደግሜ ደግሜ አነበብኩት እጅግ የሚመስጥ ገለጻ ነው:: እስቲ ትንሽ ቀንጨብ አድርጌ ማጓጓያ ላቅርብ:

በቅርቡ በአፍሪካ ክለቦች ቻምፒዮንስ ሊግና በኮንፌዴሬሽን ዋንጫ የኢትዮጵያዎቹ ቡናና ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሰሜን አፍሪካዎቹ ተጋጣሚዎቻቸው ጋር ከሜዳቸው ውጪ ያደረጓቸው ጨዋታዎችን ካየሁ በኋላ በፍጥነት አእምሮዬ ላይ የመጣብኝ ነገር ቢኖር “የኢትዮጵያ እግርኳስ ተጨዋቾች የሚያንሳቸው ነገር ቁመት፣ ጉልበትና የኳስ ችሎታ ሳይሆን ያላቸውን ነገር እንዴት መጠቀም እንዳለባቸውና ኳስ ተጋጣሚያቸው እግር ውስጥ ስትገባ ምን ማድረግ እንዳለባቸው አለማወቃቸው ነው” የሚለው ነበር።
ብዙውን ጊዜ በክለብና በብሄራዊ ቡድን ደረጃ የኢትዮጵያ ቡድኖች ከውጪ ቡድኖች ጋር ከተጫወቱ በኋላ የተጋጣሚ ቡድኖቹ አሰልጣኞች ስለኢትዮጵያ ቡድኖች የሚሰጡት አስተያየት ተመሳሳይ ነው፤ “ጥሩ የኳስ ችሎታ አላችሁ” በሚል ይጀምርና “ግን…” ብሎ በሚቀጥል አረፍተ-ነገር የሚጠናቀቅ። “ግን…” ብሎ የሚቀጥለው አስተያየት ቀሪዎቹን አንድ ቡድን ሊኖረው የሚገቡትን ብቃቶች የሚያጠቃልሉ ናቸው።

እንደኔ የእግር ኳስ ፍቅር ካሎት ቀሪውን ትይይዙን ጠቅ በማድረግ ግንዛቤዎን ያዳብሩበት::ዛሬ የምወደው ባርሴሎና ከማልወደው ሪያል ማድሪድ ይጫወታል ድል ለባርሳ እያልኩ የፍሰሀን ምልከታ በተግባር ለማስተዋል ይመቻል እና ተደሰቱበት::

የኢትዮጵያ ብሎጎች ምን ጻፉ?

የሀገራችን መገናኛ ብዙሀን አውቀው በፍርሀት ሳያውቁ በስህተት ጆሮ ዳባ ያሏቸውን ሀገራዊ ጉዳዮች ለማንበብ ፡ ለመስማት አማራጩ ፌስቡክ ትዊተር እና የተለያዮ ብሎጎች እየሆኑ መምጣታቸውን ለማወቅ አዲስ አበባ በየጥጋ ጥጉ ያሉ የኢንተርኔት ካፌዎችን ለደቂቃ መጎብኝት በቂ ነው:: በሳምንቱ ማን ምን ከተበ? ምን አስደመመው? ምን ተነተነ?ምን አሳዘነው? ምን አስደሰተው? የሚለውን በአጤሬራ መልክ ማቀመስ ደግሞ ባይጠቅምም አይጎዳም ስለዚህ ባሳለፍነው ሰሞነ ህማማት ኢትዮጲያውያን የፌስቡክ የትዊተር እና የተለያዮ ብሎግ ተጠቃሚዎች ምን አሉ? በምን ተደሰቱ ? በምን አዘኑ? በምንስ ተማረሩ? እንደተለመደው ከብሎግ ክለሳ እጀምራሁ:: ተከተሉኝ፦

ከእንጨት መርጦ ለታቦት ከብሎግ መርጦ ለትኩረት ልበልና እስቲ ቀልቤን የሳቡኝን ላካፍላችሁ:: በዚህ ሳምንት የተስፋዬ ገብረአብ ብሎግ የቅዳሜ ማስታወሻ በመጋቢት ወር ከደቡብ ክልል የተፈናቀሉ ዜጎችን አስመልክቶ ምሁራን በተለይ በውጪ ያሉ ከተለያዮ አንግሎች አንጻር የሰጡትን አሰተያየትና የሀገሪቱን እጣ ፈንታ የራሱን ምልከታ ጨምሮ አስነብቦናል:: የጽሁፉ የመጨረሻው መስመር ገለልተኛ ስለመሰለኝ እዚህ ልጥቀስላችሁ እንዲህ ይላል ፦

የቆየውንና ጊዜው ያለፈበትን በጥላቻና በጀብደኝነት ላይ ተመስርቶ የነበረውን አንድነት በመተው፣ ሰብአዊነትንና እኩልነትን ባረጋገጠ መልኩ ኢትዮጵያዊነትን መገንባት ይገባል!

መቼም ገለልተኛ ምናምን ያልኩበትን መንፈስ ትረዱልኛላችሁ:: ቀሪውን እናንተው እዚህች ላይ ጠቅ ያአድርጉ እንዲህም ይባላል ለካ ታስብሎታለች:: የቅዳሜ ማስታወሻ ለግዜው ኢትዮጵያ ውስጥ አልታሸገም::

ቀጠልኩ ወደ አቤ ቶክቻው:: ከዚህ ሳምንት የአቤ ጽሁፎች ቀልቤን የሳበችው የፀሎተ ሀሙስ እለት ያተማት የትላንት በያይነቱ የምትለዋ ጽሁፉ ናት:: ፌስቡክ ላይ ሞቅ በለው የሰነበቱ ወሬዎችን በአጤሬራ መልክ በሀዘን በደስታ እንደገና በሀዘን ካዛ ደግሞ በሽሙጥ ከራሱ ስሜት ጋር አዋዝቶ አቅርቧል:: ትንሽ ልጥቀስ፦

“እምዬ ኢትዮጵያ የጀግኖች እናት እስቲ ፈልጊልኝ የሚከራይ ቤት” የሚል ፅሁፍ ተለጥፎ አየሁ። ይህንን ፅሁፍ ከዚህ በፊትም አይቼዋለሁ። እውነትም የሚከራይ ቤት እንኳ ኢትዮጵያችን ብታገኝልን ቢያንስ በየ አረብ ሀገራቱ እህቶቻችን አየሰቃዩም ነበር። ብዬ እያሰብኩ… ወረድ አልኩ። አሁን አሪፍ ዜና አየሁ። እስክንድር ነጋ ታላቅ አለም አቀፋዊ ሽልማት አገኘ!
ታዋቂው እና ተወዳጁ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ “ፔን ኢንተርናሽናል” ከተባለ ድርጅት PEN/Barbara Goldsmith Freedom to Write Award. የተባለውን ሽልማት አገኝቷል።

እስክንድር ነጋ የ PENንን ሽልማት ማግኘቱ በዚህ ሳምንት እጅግ በርካታ ኢትዮጵያዊያንን አስፈንድቋል:: ዜናው እንደተሰማ ዜናውን ያበሰሩትን ደረገጾች ትይይዝ በየፌስቡክ ገጾቻቸው ለጣጥፈዋቸው ነበር:: ብዙዎቹም ዜናውን መውደዳቸውን likeን ጠቅ በማድረግ ገለጸዋል:: መቼም እንዲህ አይነቱን ዜና አዲስ ዘመን ላይ ማንበብ እንዴት እንደምናፍቅ:: ለማናቸውም እኔም ደስ ብሎኛል:: ይገባዋልም::

ከወርሃ የካቲት ጀምሮ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎችን ትኩርት ስቦ የነበረው በዋልድባ ገዳም ዙሪያ የተነሳው ውዝግብ ነው:: በዚህ ሳምንት ሚያዚያ 1 ፤ 2004 ዓ.ም አንድ አንድ አድርገን የሚባል ብሎግ አስገራሚ ሊባል የሚችል ዜና አስነብቦናል:: ከመጀመሪያው አንቀጽ፦

አባቶች በጸሎት እየበረቱ ይገኛሉ ፤ አሁን በደረሰን መረጃ መሰረት በቦታው ላይ ያለው ስራውን የሚያከናውን ተቀጣሪመሃንዲስ ባልታወቀ ምክንያት ሞቷል ፣ ስው ለመስራት የተቀመጡ የኮንስትራክሽን ማሽነሪዎቹ በየሰአቱእየተበላሹይገኛሉ ፣ ካልታወቀ ቦታ የተለያዩ አውሬዎች እየወጡ ሰራተኛን መተናኮል ጀምረዋል::

ከስፖርት ብሎጎች የፍሰሀ ብሎግ ዛሬ ደግሞ ስለተወዳጇዋ ደራርቱ “ሳቂታዋ የረጅም ርቀት ሩጫ ንግስት” በሚል ርእስ በጣፋጭ ቋንቋ ያወገናል:: በአዲስ አበባ FM ራዲዮኖች በእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ እንጨት እንጨት ያለ ዘገባ ለተሰላቸ ምነኛ ምርጥ አማራጭ ነው:: የሀገራችንን የአትሌቲክስ ጀግኖች ያልተነገሩ ታሪኮች እንዲህ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ፈልፍሎ የሚያቀርብልን አጠተን ተሰቃየን የሚሉ ጓደኞቼ በርካቶች ናቸው:: ከመጀመሪው አንቀጽ፦

ኦሎምፒክ ምን እንደሆነ ከማወቄ በፊት የእሷን ስምና ድሏን ነበር የማውቀው። ስሟ በሬዲዮ በተደጋጋሚ ሲጠራ ስለሰማሁት አእምሮዬ ውስጥ ተቀርጾ ተቀምጧል። “የኦሎምፒክ ወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት ሆነች” የሚለው ጩኸት ልቤን አልሰረቀውም፤ ልጅ ነበርኩና የኦሎምፒክን ዋጋና ምንነት ባለማወቄ። “ሮጣ ተፎካካሪዎቿን እንደ ጭራ ከኋላ አስከትላ አሸነፈች” የሚለው ድምጽን ለማስተናገድ ግን አልተቸገርኩም። ምክንያቱም እየተሯሯጠና አቧራ እያቦነነ ለነበረ ልጅ ሩጫ፣ መቅደምና መቀደም ምን እንደሆኑ ለይቶ ለማወቅ አያስቸግረውምና።

ቀሪውን እዚህ ላይ ጠቅ አድርገው ያንብቡ:: በመጨረሻም ከራሴ ብሎግ ስለልማታዊ ጋዜጠኝነት የጻፍኩትን እንካችሁ:: መልካም ፋሲካ::

በኢትዮጵያ ያለው ልማታዊ ጋዜጠኝነት ወይስ የጋዜጠኝነት ጣረ ሞት?

በዚህ ጽሁፍ የማቀርብላችሁ ርእሰ ነገር ልማታዊ ጋዜጠኝነት በኢትዮጵያ የሚል ነው:: አዲስ ጉዳይ መጽሄት ሰሞኑን በተከታታይ እትሞቿ ስለ ልማታዊ ጋዜጠኝነት የተላያዩ ሰዎችን ሙግት ይዛ ቀርባ ነበር:: መጽሄቷ አንጋፋ የጋዜጠኝነት መምህር የሆኑትን አቶ ማእረጉ በዛባህን ቃለ መጠይቅ በማድረግ እና በመቀጠልም የኝህኑ መምህር ጽሁፍ አንዳንድ ነጥቦች ስለ ልማታዊ ጋዜጠኝነት በሚል ርእስ ለአንባቢ አቅርባለች:: ከቃለ መጠይቁም ሆነ ከቀረበው ጽሁፍ በመነሳት በሀገራችን ልማታዊ ጋዜጠኝነት የሚባለው የጋዜጠኝነት ዘውግ እየተተገበረ ነው ማልት ያዳግታል የሚል ድምዳሚ ላይ እንደርሳለን:: በእውነቱ ከሆነ የአቶ ማእረጉ አቋም የኔም አቋም ነው:: ነገር ግን በዚህ በሳቸው ጽሁፍ አነሳሽነት ሁለት ከጋዜጠኝነት ሙያ ጋር ዝምድና ያላቸው ወጣቶች የለም የአቶ ማእረጉ ድምዳሜ ስህተት ነው ይሉናል :: እንዳውም አቶ ማእረጉ ሆነ ብለው እውነታን ለመካድ በመሻት ልማታዊ ጋዜጠኝነት በኢትዮጵያ የለም የሚል የተሳሰተ ድምዳሚ ላይ ካልደረሱ በቀር ኢትዮጵያ ውስጥ ሊካድ በማይቻል ሁኔታ የልማታዊ ጋዜጠኝነት ውስን ዘውጎች በመንግስት መገናኛ ብዙሀን እና በአንድ አንድ FM ራዲዮን ጣቢያዎች እየተተገበሩ ናቸው ሲሉ የክርክር ነጥባቸውን አቅርበዋል:: ይህ የነዚህ ሁለት ወጣቶች አቋም የነሱ ብቻ አቋም አድርጌ አልመለከተውም:: የመንግስትም አቋም እንደሆነ አምናለሁ:: አለመታደል ሆኖ እንጂ መንግስት ለዲሞክራሲ መጎልበት እንዲህ መሰረታዊ ፋይዳቸው ላቅ ያሉ ጉዳዮችን አደባባይ አውጥቶ ሕዝባዊና ምሁራዊ ክርክሮች እንዲካሄዱ ከመፍቀድም አልፎ ሁኔታዎችን ማመቻቸት ነበረበት ግን አልሆነለትም፤ ወደ ምክንያቶቹ አልሄድም የጽሁፌ ትኩረት አይደለምና። የግል መገናኛ ብዙሃንም ቢሆኑ ጥቂቱ በሀገር ውስጥ ግማሹ ከሀገር ውጪ በመሆን እንዲህ ያለውን ጉዳይ በተንጠባጠበ እና አልፎ አልፎ በሚነሳ የአምድ ማሟያነት ከክርክር ባለፈ ጉዳዩን በጥልቀት በመመርመር የፖሊሲ አቅጣጫዎችን ለመጠቆም በሰፊው ለመስራት በሞከሩ ነበር: ምንም እንኳ የእስካሁኑ ሙከራቸው ቢያስመሰግናቸውም: :

በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ልማታዊ ጋዜጠኝነት ነው/አይደለም የሚለው ክርክር በልማታዊ ጋዜጠኝነት ሀልዮቶች ላይ የተንጠለጠለ መሆን የለበትም:: በእርግጥ የ”ልማታዊ” ጋዜጠኝነት ሀልዮቶችን ፋይዳ እና መገለጫዎቹን የ”ልማታዊ” ጋዜጠኞችን ስነ ምግባር እና ሌሎችንም ከርእሰ ጉዳዩ ጋር ቅርበት ያላቸውን ዝርዝር ጉዳዮች በሙሉ መነጋገርም መወያየትም ተገቢ ነው:: ነገር ግን ይህን የመሰለ ሀገራዊ አብይ ጉዳይ በሃልዮት ደረጃ ብቻ ተወያይቶ ወይም “ምናምን” ብሮድካስት ኮርፖሬሽን፤ በሚባለው ራድዮ ጣቢያ አንዳንድ ፕሮግራሞች ላይ ምንትስ ስለሚባል ሰፈር ወጣቶች ድህነትትን ለመዋጋት በማሀበር ስለመደራጀታቸው ሰምቻለሁ::ምንትስ በሚባለው FM ራድዮ ዜጎች ያለ ፍራሃት በስነተዋልዶ ጤና ሲወያዩ ሰምቻለሁ :አይቻለሁ :: ስለዚህ በኢትዮጵያ ውስጥ እየተተገበረ ያለው ልማታዊ ጋዜጠኝነት ነው ብሎ አፍን ሞልቶ ማውራት ይችላል ለሚሉ ባልዳረባዎቼ : እኔ ልላቸው የምቸለው ነገር ቢኖር እነዚህ የክርክር ነጥቦች የየዋህነት ካላያም የጅለነት ወይም ድግሞ አውቆ የተኛ አይነት የመካራከሪያ ነጥቦች ናቸው:: ምክኒያቱም ልማታዊ ጋዜጠኝነት በሃልዮት ደረጃ እንኳ በቅጡ ያልተደላደለ ወጥ የሆነ የጋዜጠኝነት ስነ ምግባር የሌለው ከምእራባዊያን የጋዜጠኝነት ባህል እንኳ በምን እንደሚለይ ጥርት ባለ ሁናቴ ሳይታወቅ: በኢትዮጵያ ውስጥ እየተተገበረ ያለው ልማታዊ ጋዜጠኝነት ነው ብሎ በችኮላ ከመደንገግ በፊት: የሀገራችንን የሚዲያ መልእካ፡ምድር(Media Landscape)፣ ህጋዊ ዳራቸውን እና ጋዜጠኞቻችን ሙያቸውን እየተገበሩ ያሉበትን አውድ በሚገባ ዘርዘር አድርጎ ማየቱ ይቀድማል ብዬ ሰለማምን ነው::ከዚህም ባሻገር የመገናኛ ብዙሃን የስራ ባህል እና የጋዜጠኝነት ልምድ ትንተና ባንድ አገር ውስጥ ካላቸው ተጨባጭ ኹኔታ ነው መጀመር ያለበት። እስቲ ተጨባጩን የአገራችንን የመገናኛ ብዙሃን የስራ ባህል እና የጋዜጠኝነትን ስራ አንኳር ነጥቦች በወፍ በረር እንቃኛቸው፦

በሀገራችን የሚዲያ መልእካ፡ምድር ላይ የሚገኙትን እድሜ ጠገብ እና ሰፊ ጂኦግራፊያዊ ተደራሽነት ያላቸውን የመገናኛ ብዙሃን ፦ኢቴቪ፡የኢትዮጵያ ራዲዮ እና አዲስ ዘመንን ጨምሮ በየክልሉ የሚገኙትን የመገናኛ ብዙሃንን በባለቤትነት የሚያስተዳድረው መንግስት ነው:: ይህም በአዋጅ የተረጋገጠለት መብቱ ነው:: ነገር ግን መንግስትም ይሁን ግለሰብ በባለቤትነት የሚያስተዳድረው የትኛውም የመገናኛ ብዙሃን ደግሞ ኢኮኖሚያዊ ትርፍን ከማጋበሻነት በተጨማሪ የባለንብረቱን የፖለቲካ አቋም ማራመጃ ለመሆን ምቹ ነው:: በዚህ ጉዳይ ላይ የመገናኛ ብዙሃንን የፖለቲካ፡ኢኮኖሚ(Poletical Economy of the Mass Media) በመተንተን እውቅ የሆኑት ኖኦም ቾምስኪን እና ኤድዋርድ ሄርማን በ 1988 “ይሁንታን ማመረት”(Manufacturing Consent: The Political Economy of the Mass Media) በሚል ርእስ ካሳተሙት መጻህፍ የፕሮፓጋንዳ ሞዴል የሚለው ጽንሰ ሀሳብ የሀገራችንን የመገናኛ ብዙሃን መልእካ፡ምድር እና የፖለቲካ፡ኢኮኖሚ በደንብ አድምቶ ስለሚገልጽልኝ ዋቤ ዕድርጌ ከዚህ እንደሚከተለው እጠቀስዋለሁ(ትርጉም ራሴ)፦

መሰረታዊ የሀብት እና የፖለቲካ ስልጣን ክፍፍል መዛነፍ በሰፊው በሚስተዋልባቸው ሀገራት መገናኛ ብዙሃን ስልታዊ በሆነ ዘዴ የሚስተዋለውን እለመመጣጠን የማድበስበስ ታላቅ ሚናን ይጫወታሉ:: በተለይም የስልጣን መዘውሩን የሚቆጣጠሩት ጥቂት ቢሮከራቶች ከሆኑ እና ሞኖፖላዊ የመገናኛ ብዙሃን ቁጥጥር የሰፈነበት ስራዕት ከሆነ በተለይ ደግሞ ህጋዊም ሆነ ህገ ወጥ (ጭማሪ ከራሴ) የቅድመ ምርመራ አሰራርን የሚያበረታታ ከሆነ የመገናኛ ብዙሃን ስልጣን ላይ ለሚገኙት ልሂቃን ጥቅማቸውን ማስጠበቂያ መሳሪያ መሆናቸው ሳይታለም የተፈታ ነው:: (ገጽ 1 1988)

ይህ ማለት ደግሞ መንግስታት የህዝቡን አስተያየት በመገናኛ ብዙሃን በኩል በሚገባ ለመቆጣጠር እንዲያመቻቸው እድል ይፈጥርላቸዋል ማለት ነው:: በዚህም መሰረት መንግስታት በቁጥጥራቸው ስር የሚገኙትን መገናኛ ብዙሃን በመጠቀም ህዝቡ ወይም ጋዜጠኛው በራሱ ተነሳሽነት የመረጠውን ርዕሰ ጉዳይ ወይም በወቅቱ እየሆነ ያለውን እንገግጋቢ የመገናኛ ብዙሃንን ትኩረት የሚሻ ጉዳይ ወደ ጎን በመተው የራሳቸውን እጀንዳ ማራጋቢያ እና የኢኮኖሚ ጥቅም ማስጠበቂያ ያረጉታል ማለት ነው::

ለጥቄ ይህንን በምሳሌ ላስረዳ ተከተሉኝ ::በሀገራችን የሚዲያ መልእካምድር ላይ ከላይ ከጠቀስኩት የቾምስኪ እና የሄርማን ሀልዮት አንጻር በግሉም ሆነ በመንግስት የመገናኛ ብዙሃን የሚስተዋሉ የባለቤትነት ቁጥጥር ምሳሌዎችን በደምሳሳው ልጠቃቀስ:: ላካሄድ እንዲያመቸን ከስርጭት ሽፋን ተደራሽነት እና ስለ መንግስት መገናኛ ብዙሃን በአይነ ህሊናችን ስናስብ ሁልዜም ድቅን ስለሚልበን የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ፊት እውራሪ ከሆነው ኢቴቪ ልጀምር:: መንግስት ኢቴቪን ልክ እንደ ሀረር ሰንጋ ገመድ በእንገቱ ላይ አስሮ ወደ ፈለገበት እንደሚነዳው ከሚያሳብቅበት የመገናኛ ብዙሃን ቀዳሚው ነው:: በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ላይ የፍልስፍና ዲግሪ ጽሁፋቸውን የጻፉት ኖርዊያዊው ቴርዬ ስካርድል (Terje S. Skjerdal) በ 2008 “Conflicting professional obligations among government journalists in Ethiopia” በሚል ርእስ ካሳታሙት የጆርናል ጽሁፍ በመጥቀስ የክርክር ነጥቤን ላጠናክር ለነገሩ የኢቴቪን የመንግስት አፍነት ለማስረዳት ምስክር መጥቀስ አያሻውም:: ከወቀሳ ለመዳን ግን (Terje) ቴርዬ የጆርናል ጽሁፍን ሲጽፍ በማስረጃነት የተጠቀመውን ስሙ እንዲጠቀስ ያልፈለገ የኢቴቪ የእንግሊዝኛ ዴስክ ከፍተኛ ረፖርተር በህዳር 2000 ዓም የኢትዮጵያ የፕሬስ አዋጅ ከመጽደቁ በፊት ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሞት ስለነበረው የፕሬስ አዋጅ የተቃውሚ ድምጾችን ያካተተ የዜና ዘገባ በመስራቱ በወቅቱ የማስታወቂያ ሚንስቴር ከነበሩት ከአቶ በረከት ሰሞኦን የደረሰበትን ጫና እንዲህ ያስረዳል (ትርጉም ከራሴ)፦

“የፕሬስ አዋጁ በጣም አፋኝ ነው የሚል እስተያየት የሚሰጡ ብርካታ ሰዎች እራሱ አቶ በረከት ሰሞኦን በሚመራው በፕሬስ አዋጁ ዙሪያ በተዘጋጀ የውይይት መድረከ ላይ በሰፊው ይደመጡ ነበር:: በመሆኑም በማታው የዜና እወጃ ሰአት በዚህ ዙሪያ ባዘጋጀሁት የዜና ዘገባ ላይ የነዚህን ሰዎች እስተያየት አካትቼ አቀረብኩ::”

“በማግስቱ ግን እዛው ኢቴቪ ህንጻ ላይ ይገኝ ከነበረው ሚንስትር መስሪያ ቤቱ ስልክ ተደውሎ ተጠራሁ:: ሚንስትሩ በሰራሁት የዜና ዘገባ ተበሳጩብኝ:: ለምንስ እንዲህ እይነት ዜና እንደሰራሁ ጠየቁኝ:: እኔም ዜናው ባላንስ እንዲኖረው ወይም ሚዛናዊ እንዲሆን ነው ስል ያለ ምንም ፍርህት ላስረዳችው ሞከርኩ:: እሳቸው ግን ይህ የባላንስ ወይም የሚዛናዊነት ጉዳይ አይደለም:: ይህ የመንግስት መገናኛ ብዙሃን እንደ መሆኑ መጠን መስበክ ያለብህ ሰለመንግስት ነው:: አሉኝ”::(ገጽ 6 2008)

ሌላ ምሳሌ ልጨምር:: መሀመድ ሰልማን በ2011 ፒያሳ መሃሙድ ጋር ጠብቂኝ በሚል ርእስ ካሳተመው የወጎች እና የመጣጥፎች መድብል መንግስት በመገናኛ ብዙሃን ላይ ያለውን ቁጥጥር እና የቾምስኪን እና የሄርማንን ሀልዮት ሰነ ጽሁፋዊ ለዛ ባለው መንገድ ሰለሚያስረዳልኝ ኢቴቪ እና ተዛማጅ ትዝታዎቼ ከሚለው መጣጥፍ የኢቴቪ የዜና ቀመር የሚለውን ቃል በቃል እንደሚከተው ገልብጨዋለሁ::

ኢቴቪ አንድን ዜና ዘለግ ላለ ጊዜ እያቦካ የመጠቀም ባህል አለው:: ለምሳሌ ከአላማጣ ማይጨው መንገድ ሊሰራ ነው ብለን ብናስብ ከሚሰራው መንገድ ይልቅ ዜናው እንደሚረዝም በዚህ መልክ ማየት እንችላለን:: በትንሹ ከአንድ መንገድ አስር ዜናዎች ይፈለፈላሉ

1.ከአላማጣ ማይጨው የሚደርሰውን የጠጠር መንገድ ወደ አሥፋልት ለማሳደግ የሚያስችል ብድር ከቻይናው ማክሲም ባንክ ተገኘ።
2.ከአላማጣ ማይጨው የሚደርሰውን የሚገኘውን መንገድ ለመስራት ከቻይናው ሲራቢሲ ኩባንያ ጋር ስምምነት ተካሔደ::
3.ከአላማጣ ማይጨው የሚወስደውን መንገድ ለመጀመር የመሰረት ድንጋይ ተጣለ::
4.ከአላማጣ ማይጨው የሚወስደው መንገድ ግንባታ ተጀመረ::
5.ከአላማጣ ማይጨው የሚወስደው መንገድ ግንባታ እየተፋጠነ ነው ተባለ::
6.ከአላማጣ ማይጨው የሚወስደው መንገድ ግንባታ በመጓተቱ ነዋሪዎች ተቸገርን አሉ::
7.ከአላማጣ ማይጨው የሚወስደው መንገድ ግንባታ 65 በመቶው ተጠናቀቀ::
8.ከአላማጣ ማይጨው የሚወስደው መንገድ ግንባታ በተያዘለት የጊዜ ገደብ ይጠናቀቃል ተባለ:
9.ከአላማጣ ማይጨው የሚወስደው መንገድ ግንባታ ተጠናቀቀ::
10.ከአላማጣ ማይጨው የሚወስደው መንገድ ግንባታ በመጠናቀቁ: የአካባቢው ነዋሪዎች ደስታቸውን ገለጹ::

ሰፊው የኢትዮጵያ ህዝብ አንድ ዜና በ10 ተመንዝሮ ሲቀርብለት 10 ጎዳናዎች የተሰሩለት ስለሚመስለው “ይህ መንግስት ምነኛ ልማታዊ ነው” ሲል ይገረማል::”(ገጽ 73/74 2004) ይህዝብ ይሁንታን ማምረት ይሉሃል ይህ ነው:: ውዱ ባልደራባዬ መሀመድ ሆይ የኖኦም ቾምስኪን እና ኤድዋርድ ሄርማን የፕሮፖጋንዳ ሞዴል ኢትዮጵያዊ በሆነ ትንትና ለማስረዳት ስራዪን ምነኛ አቀለልክልኝ::

ከዚህ ባሻገር የመንግስት ጠንካራ የባለቤትነት ቁጥጥር በከፍተኛ ሁኔታ የሚስተዋልበት ከቅርብ ግዜ ወዲህ እንደ የአዲሱ ዘመን የመገናኛ ብዙሃን አውታር የሚቆጠረው የቴሌኮሚኒኬሽን አገልግሎት ነው:: ከቴሌኮም አገልግሎቶች መሃከል የሞባይል ስልክ አገልግሎት እና ሌሎችም የመረጃ መረብ ወይም የኢንተርኔት አገልግሎቶችን ከ85 ሚሊዮን በላይ ለሚሆን የኢትዮጵያ ህዝብ በብችኝነት የሚያቀርበው ዕትራፊው እና ብቸኛው የኢትዮጵያ ቴሌኮም ኮርፖሬሽን ነው:: ስለ ቴሌኮም የአገልግሎቶት ጥራት መጓደል ተጠቃሚው በሚገባ ስለሚያውቀው በዚህ ጽሁፍ ምንም አልልም:: በዚህ ላይ ተጠቃሚው ለቴሌኮም አገልግሎቶች የሚከፍለው ዋጋ እጅግ ውድ መሆኑን የ2011 የFreedom House ን ሪፖርት ጠቅሶ ነብዩ እያሱ ስደት በጋዜጠኛው አይን በሚለው አዲስ መጻሃፉ ላይ ዘግቧል:: (ገጽ 312 2004):: በአንጻሩ ግን ልማታዊ ጋዜጠኝነት በሰፊው ይተገበርባቸዋል በሚባሉት እንደ ህንድ ባሉ ሀገራት የቴሌኮም አገልግሎቶች የዜጎችን አሳታፊነት በማሳለጥ ዜጎች ለልማት ብቻም ሳይሆን ለመልካም አስተዳደር እና ለግልጽነት መጠናከር የድሮዎቹ የመገናኛ ብዙሃን ተብለው ከሚጠሩት እንደ ሬዴዮ እና ቴሌቭዝን ሁሉ ህብረተሰብን በመቅርጽ ለሀገር እድገት የማይተካ ሚና ይጫወታሉ: :

ከላይ የተቀሱት ማሳያዎች በኢትዮጵያ ሚዲያ መልእካ፡ምድር ላይ አድራጊ ፈጣሪ መንግስት መሆኑን ያረጋግጥልናል:: እላይ በጠቀስኩት የቾምስኪ እና የሄርማን ሀልዮት መሰረት ደግሞ መንግስት ከፍተኛ ቁጥጥር በሚያሳድርባችው ሀገራት መገናኛ ብዙሃን የህዝብን ይሁንታ በማመረት ስራ ነው የሚጠመዱት:: ይህንንም ስራቸውን(ይሁንታ ማመረትን) የዳቦ ስም አውጠተውለት ልማታዊ ጋዜጠኝነት ይሉታል እንጂ ልማታዊ ጋዜጠኝነት የሚባል ነገር የለም: ለኔ ባሀገራችን የሚዲያ መልእካ፡ምድር ላይ ዛሬ የሚሥተዋለው ከዚህ ብዙም የሚለይ አይደለም:: አቶ ማእረጉም ለማለት የፈለጉት ይህንኑ ይመስለኛል::እስቲ አሁን ደግሞ ልማታዊ ጋዜጠኝነት ከኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙሀን ህግ ምን ይላል::

ልማታዊ ጋዜጠኝነት ከህግ አንጻር ያስኬዳል?

በህገ መንግስቱ አንቀጽ 29 ዜጎች ዘርፈ ብዙ ከሆኑ የመገናኛ ብዙሀን መረጃን የማግኝት እና የመሰላቸውን አስተያየት የመያዝ መብታቸው ተረጋግጦላቸዋል:: በተለይ ደግም በአንቀጽ 29 ንኡስ አንቀጽ 5 መሰረት በመንግስት ቁጥጥር ስር የሚገኙ መገናኛ ብዙሀንም እንኳ ቢሆኑ የአስተሳሰብ እና የአስተያየት ብዙሃነትን (Diversity of Expression and Opinion) ማረጋገጥ አለባቸው:: በመንግስት ቁጥጥር ስር እንዲሆኑ የተደረጉበት ምክኒያት ይህንኑ ለማድረግ ነው:: ከዚህ በተጨማሪ የመገናኛ ብዙሀን እና የመረጃ ነጻነት አዋጅ ቁጥር 590/2000 መገናኛ ብዙሀን በነጻነት ስራቸውን ማከናወን እንዲችሉ ህገ መንግስታዊ መብታቸውን በድጋሜ አረጋግጧል:: እዚህ ላይ እንዲተኮርበት የምፈልገው ነጥብ ታዲያ በመንግስት ቁጥጥር ስር የሚተዳደሩ የመገናኛ ብዙሀን እና የነዚሁ ድርጅቶች ምንደኛ ጋዜጠኞች የአስተሳሰብ እና የአስተያየት ብዙሃነትን በተግባር ለማረጋገጥ መትጋት አለባቸው እንጂ በልማታዊ ጋዜጠኝነት ስም እራሳቸውን እንደ ሀገር ገንቢዎችም ሆነ እንደ መንግስት አጋሮች በመቁጠር ህገ መንግስቱ በአንቀጽ 29 ንኡስ አንቀጽ 5 ያረጋገጠውን ዲሞክራሲያዊ መብት እንዲጣስ ተባባሪ መሆን የለባቸውም:: ከላይ ለማሳየት እንደሞከርኩት የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ትልልቅ መንግስታዊ አጀንዳዎችን ለሀገሪቱ ብቸኛ ና መለኮታዊ መፍትሄ አድርገው ያቀርባሉ መንግስትን የሚተቹ ዜጎችን ደግሞ ትችቱ ለምን እንኳ እንደተሰነዘረ ቀርበው እንዲያስረዱ ሳያደርጉ የሀገር ጠላቶች እና መርዶ ነጋሪ እንደሆኑ ተደርገው ይቀርባሉ:: ከህጉ አንጻር ግን ይህ የመብት ጥሰት እንጂ ልማታዊ ጋዜጠኝነት አይደለም:: ለኔ አንድ ጋዜጠኛ በከፍተኛ የሞያ ልቀት እና የሰነ ምግባር ብቃት ያለ መንግስትም ሆነ ያለ ቱጃር ተጽእኖ በነጻነት ስራውን ከሰራ እሱ ጋዜጠኛ ነው:: ከፈለጋችሁ ልማታዊ የሚል ቅጥያ ልትጨምሩበት ትችላላሁ::

ነጻ የግል መገናኛ ብዙሃንስ?

በግል የመገናኛ ብዙሃንም ቢሆን የተጋነኑ “ልማታዊ” ዜናዎች ባይስተዋልባቸውም:: በማስታወቂያ አስነጋሪዎች ተጽእኖ ምክኒያት ማስታወቂያዊ ዜናዎችን :ማስታወቂያዊ ዶክመንተሪዎችን እና ሌሎችንም ፕርግራሞች (Adevertorials) ማየትም መስማትም እየተለመደ መጥቷል:: በኤፍ ኤሞቻችንም ሆነ በጋዜጦቻችን አንዳንድ ዘገባዎች ላይ እነዚህን ክፉ የጋዜጠኝነት ተግዳሮቶች አልፎ አልፎ አያለሁ:: ስም ሳልጠቅስ ምሳሌ ልስጥ: አንድ ማንትስ የሚባል ወፍ ዘራሽ ቱጃር BIKS የሚባል ብስኩት ፋብሪካ በቅርቡ ከፍቷል ወይም አለው እንበል:: ይህ ወፍ ዘራሽ ቱጃር ብስኩቱን በገፍ መሸጥ ይፈልግ ስለነበር ማስታወቂያ ማሰራት ያስባል:: ከተማው ውስጥ ያሉት የማስታወቂያ ለፋፊ ድርጅቶች በደቂቃ ታይታ/ተሰምታ ለምታበቃ ማስታወቂያ ዋጋቸው የሚቀመስ አለሆለትም:: በዚህ ላይ ማስታወቂያ ማስታወቂያ ነው:: በአጋጣሚ አንድ ቀን ይህ ባለሀብት ማንትስ ልማት ማህበር ባዘጋጅው ቴሌቶን ላይ አንድ ሁልግዜ በራዲዮ ድምጹን እየሰማ ባካል ግን የማያውቀውን ትንታግ ልማታዊ ጋዜጠኛ ይተዋወቃል:: አጋጣሚውንም በመጠቀም ለልማታዊ ጋዜጠኛው ማስታወቂያ ማሰራት ፈልጎ ዋጋው አልቀመስ እንዳለው ይነግረዋል መፍትሄ ካለውም እንዲያማክረውም ይጠይቀዋል:: ጋዜጠኛውም የሆነ አካባቢ ስለሚኖሩ ምንዱባን ያአኗኗር ችግር የሚመለክት የራዲዮ ዶክመንተሪ ለመስራት እያሰብኩ ነው ይህንን ፐሮግራም በአነስተኛ ዋጋ ስፖንሰር አድርግና ስለ BIKS ብስኩት ፋብሪካ ሰፋ ያለ እና ተከታታይ የዜና ዘገባ ላቅርብልህ የሚል የልማታዊ ጋዜጠኝነት ሞያዊ ምክሩን ሰጠው:: በዚህም ተስማሙ ባለጸጋውም ከፍተኛ ከሆነ የማስታወቂያ ወጪ ከመዳኑም ባሻገር በቀላል ወጪ የኩባንያውን ስም በተጋጋሚ ማህበራዊ ችግሮችን ከሚፍቱ ልማታዊ ሀገር በቀል ኩባንያዎች ተርታ ተሰለፈለት:: ህዝቡም ይህንን ልማታዊ ባለጸጋ ላሀገር አሳቢ ለደሀ አዛኝ አድርጎ ስለሚያስበው ብስኩት ሲገዛ ሁልግዜም የ BIKSን ነው::

እዚህ ላይ ግን የማስታወቂያ አስነጋሪ ባለሀብቶች የዜና ሽፋን ስጠኝ እና ማስታወቂያ ልስጥህ ተጸእኖ የትም ሀገር ላይ ያለ ተጸእኖ ስለመሆኑ ዋቤ መጥቀስ አያሻውም ቢሆንም ግን እንደኛ የፋይናንስ ነጻነታቸው እጀግ ፈታኝ እና እስቸጋሪ የሚሆኑባቸው የግል መገናኛ ብዙሀን በሚገኙባቸው ሀገራት ማስታወቂያዊ ዜናዎችን በልማታዊ ጋዜጠኝነት ስም መስራት መፍትሄ የሌለው መሆኑን እገነዘባለሁ:: የሀገራችን በተለይ የህትመት የግል መገናኛ ብዙሃን እለት እለት እያሻቀበ የመጣውን የህትመት ዋጋ ለመቋቋም ሲሉ በዚህ አይነት ተጽእኖ ውስጥ መግባታቸው ሳይታለም የተፈታ ነው:: ነገር ግን አሁን በሀገራችን በህትመት ላይ የሚገኙትን በተለይ ከፋይናንስ ተጸእኖ ውጪ ያሉትንም ፖለቲካዊ ጫናዎች ተቋቁመው በነጻነት ያለ ፍርሀት የጋዜጠኝነት ስራቸውን ለሚሰሩ ምስጋና ቢያንሳቸው እንጂ አይበዛባቸውም:: እኔም ለስራቸው መገን እላለሁ::

ማጠቃለያ

የሀገራችንን የሚዲያ መልእካ፡ምድር በአንድ ተራራ እንመስለውና :ይህንን ተራራ ለሁለት የሚከፍል ትልቅ ሸለቆ አለ ብለን እናስብ :: ከተራራው ግርጌ እስከ ጫፉ ድረስ ያለውን ምቹ እና ገላጣ ስፍራ የመንግስት የመገናኛ ብዙሀን የሚባሉ መጥቀስ ቢያስፈልግ ፦ኢቴቪ፡የኢትዮጵያ ራዲዮ : አዲስ ዘመን : ሂራልድ: FM97.1 አሁን ደግሞ በየክልሉ ያሉ የመንግስት አዳዲስ የክልል ኢቴቪዎች እና የግል ወይም ነጻ የሚል ቦሎ ለጥፈው በልማታዊ ጋዜጠኝነት ስም በመዝናኛ እና ስፖርታዊ አደንዛዥ ወሬዎች አየሩን የተቆጣጠሩ የሰፈሩበት ሲሆን:: ተራራውን ለሁለት በሚከፍው ትልቅ ሸለቆ ውስጥ ደግሞ በመሰናክሎች የተተበተቡ ከህዝብ ጋር ለመገናኝት ወደ ተራራው ገላጣ ስፍራ ለመውጣት ሙከራ ሲያደርጉ በሸለቆው ዳር እና ዳር የቆሙ እና ሰፊውን የተራራ ከፍል የማያስደፍሩ ሰዎች መልሰው ወደ ሸለቆው የሚከቷቸው ራሳቸውን የነጻው ፕሬስ አባላት እያሉ የሚጠሩ በተራራው ገላጣ ስፍራ የሚገኙት ደግሞ የግል ሚዲያ እያሉ የሚጠሯቸው የሚገኙበት የተራራው ክፍል ነው:: በዚህ አይነት ሀገራችን የሚዲያ መልእካ፡ምድር ታዲያ ሊኖር የሚችለው ልማታዊ ጋዜጠኝነት ወይስ የጋዜጠኝነት ጣረ ሞት?

የኢትዮጵያ ብሎጎች ምን ጻፉ?

በዚህ ሳምንት በእንሊዝኛም ሆነ በአማርኛ ብዛ ያሉ አንጅት አርስ የሆኑ ጽሆፎች፡ትንተናዎች እና ቃለመጠይቆች በኢትዮጵያ ብሎጎች (ጦማሮች) ተነበዋል። የእንሊዝኛውን ወደ በኋላ እመጣበታለሁ አሁን ቀልቤን ውደ ሳቡት የዚህ ሳምንት የጦማር ጽሆፎች ልለፍ። በነገራችን ላይ ብሎግ የሚለውን የእንግሊዘኛ ቃል ጦማር ብሎ ማን ወደ አማርኛ እንደተረጎመው ባላውቅም ቃሏ ግን ተመችታኛለች በመሆኑም ከዚህ በኋላ በቋሚነት ጦማር የምትለዋን ቃል ብሎግ በምትለዋ እንድትተካ ተወዳጅ የአማርኛ ጦማሬያንም ቢጠቀሙባት:: ካልኩ በኋላ ወደ ክለሳዪ ልፍጠን::

ባለፈው ሳምንት የኢትዮጵያ ጦማሮች ምን ጻፉ? በሚል ርእስ በጻፍኩት ክለሳ ኣንድ የፌስቡክ ወዳጄ እንዲህ ብሎኝ ነበር::
“እንግዲህ እየቃረምክ በ”አጤሬራ” መልክ አምጣልን:: አደራህን አቤ ቶክቻውን እንዳትረሳብኝ:: ልክ ምርጥ ሽሮ ወጥ ሲሰራ መከለሻ ይጨመራል አይደል? የአቤ ቶክቻውም እንደዚያው ነው:: ምርጥ መከለሻ ሆኖ ጽሑፍህን ያጣፍጥልሃል: አቤ ቶክቻው በአሸባሪነት ከተመዘገበ ግን ወንድሜ አንብበው እንጅ እንደ መረጃ ተጠቅመህ አትጻፈው::” ምክሩን ተቀብያልሁ።አቤ ቶክቻው በአሸባሪነት ስላልተፈረጀ ግን ከአቤ ልጀምር፦

በነገራችን ላይ አቤ በዚህ ሳምንት አልተቻለም። ያውም በሁለት ጦማር እኮ ነው። ለሀገር ውስጥ እና ለዳያሰፖራ አንባቢዎች፡ እንደ አይጥ በሁለት ጉድጓድ እየተጫወተ ነው። እሁድ ለት “ታላቁን” የህዳሴ ግድብ ምስራታ ምክንያት በማድረግ “ዕርቲስቶች”ዕርቲስቶች እና ፖለቲከኞች የእግር ኳስ ውድድር ኣካሂደው ነበር:: ይህንን በማስደገፍ አቤ እግር ኳስን በብሎግ ይመልከቱ በሚል ርእስ ያስነበበው ጽሁፍ በዛ ቁም ነገሮች በውስጡ ኣምቆ ይዟል:: ኣባይ የሚባለውን ተጫዋች ህዝቡ ቢውደውም ኣሰልጣኙ ወደ ጨዋታው ያስገቡት ዘግየት በለው ስለሆነ ተጫዋቹ ትንሽ የመደናገር ባህሪይ ይታይበታል ይለናል አቤ፦

ተመልካቾቻችን አሁን ኳስ ለአባይ ደርሳለች። አባይ ኳሷ ድንገት ስለደረሰችው የተደናገጠ ይመስላል። ኳስ ከያዘ በኋላ ሜዳው ላይ ባልተለመደ መልኩ ሚሊኒየም የሚል መለያውን ቀይሮ ህዳሴ የሚል ሌላ መለያ ለብሷል። በእውነቱ ይሄ የሚያስቅ ነው። ኳስ አመታቱም ግራ የሚያጋባ ነው አንድ ግዜ አምስት ሺህ ሌላ ግዜ ደግሞ ስድስት ሺህ ይለጋል። ኦያያያ… አባይ ምንም አልተዘጋጀም። ኢህአዴግ አሁን አባይን እንደ ራሱ ተጫዋች እየቆጠረው ነው። አታለል… ኢህአዴግ አታለል!!! ህዝቡም በአባይ አጨዋወት ግራ ቢጋባም ተወዳጅ ተጫዋች በመሆኑ እየዘመረለት ይገኛል። ኦ ያያያ… የኢህአዴግ አጨዋወት ግራ ነው የሚያጋባው። ተመልካቾቻችን ጨዋታው እንደቀጠለ ነው። የኑሮ ውድነቱ ኳሷን እንደያዘ ነው። በመከላከል ረገድ የህዝቡ አለኝታ የሆኑ ሃይማኖቶች አሁንም ከኢሃዴግ አጥቂዎች ተደጋጋሚ ጥቃት እየደረሰባቸው ይገኛል። ከህዝቡ ወገን የነበሩ አንዳንድ “ሀብቴ የህዝብ ፍቅር ነው” ሲሉ የነበሩ አርቲስቶች ከኢህአዴግ ጎን ተሰልፈዋል።
አቤ ይህንን እና ሌሎች በርካታ ጽሆፎችን በሁለቱ ጦማሮች ኣስኮምኩሞናል:: እዚህ ጋር ተጨነው ፍታ በሉባቸው::

ስደት በየፈርጁ፥ በአካል፣ በቅዠት፣ በሆድ፣ በመንፈስ ፣ በትዕቢት በሚል የስደት እና የኢትዮጵያውያንን ኣስከፊ ግንኙነት ኣቤል ምሁራዊ ኣስተያዩትን ዘርዘር ባለ ጸሁፉ ኣስቃኝቶናል። የራሶዎትን ኣስተያዩት ከዚህ ጻሃፊ ኣንጻር ለመለካት ከፈለጉ ይህችን ትይይዝ ጠቅ ያድርጓት::

ተስፋዬ ገብረአብ ብሎጉ ኢትዮጵያ ውስጥ መከፈት ኣለመከፈቱን የፌስቡክ ወዳጆቹ ኣንዲያጣሩልት በፌስቡክ የጠየቀው በዚህ ሳምንት ወደ ጎንደር የህክምና ሳይንስ ኮሌጅ ለማስተማር የመጣ አንድ ጀርመናዊ ሃኪም አንዲት የገበሬ ሚስት እያከመ ከባልየው ጋር እሰጣ ገባ የገጠሙበትንጉዳይ የበጌምድር ገበሬ የክብር ጉዳይ ከኛ ዘመን ትውልድ ጋር የመንፈስ ዝምድና ይኖረዋል ለማለት ቃጥቶኝ አያውቅም። ይላል ተስፋዬ ሙሉውን ጽሁፍ ለማግኘት እዚህ ላይ ጠቅ ያድርጉ:: በነገራችን ላይ ስለ ብሎግ መከፍት ስናወራ ባለፈው ሳምንት ታግድው የነበሩት ብሎጎች መለቀቃቸውን በማስመልከት ኣቤም ኣንድ ብሏል:: በነካ እጃቻው ሌሎችንም የታግዱ ድረገጾች ቢለቁልን። ይህን የምለው ግን ለራሳቸው ብየ ነው:: እኔማ በጓሮም ቢሆን እየገባሁ
ኣነባቸዋለሁ::
ሌላው በዚህ ሳምንት ከተነበቡ ብሎጎች ከፍተኛ ተደማጭነት እያገኝ የመጣውን የድምጻዊ ጃሉድን ቃለመጠይቅ ያቀረበው ሽገር ትሪቡን የሚባለው ብሎግ ነው:: የድምጻዊውን የህይወት ውጣ ውረድ በሚገባ ያስቃኞታል:: ኣንብቡት::

እንዲህ እንደዛሬው በርካታ የስፖርት ጋዜጠኞች ሳይበራከቱ በኤፍኤም አዲስ ብዙ የአዲስ አበባ ኗሪዎች ጣፍጭ ስፖርታዊ ወሬዎችን እጅግ በተደራጀ ሁኔታ ሲያቀርብ ፍሳሀ ተገኝን ብዙዎች የምታስታውሱት የናፈቃችሁም ይመስለኛል:: ግን ደግሞ አይዞን ፊሽ በሚጣፍት ቋንቋ ለዛ ያላው ያኣትሌቲክስ፡ የእግር ኳስ ፡ እና የሌሎችንም ስፖርቶች ዘገቦች በብሎጉ ያቅርብላቹኋል:: በዚህ ሳምንት ጃፓናውያን ሴቶች በፍቅር ስላበዱለት የማራቶን ጀግና አበበ ቢቂላ ያሰነብባቹኋል:: ለነገሩ ይነግራቹኋል ብል ይቀለኛል:: ስታነቡት የሚያንብላችሁ ያህል ነው የሚሰማችሁ:: ከመግቢያው፦

በአንድ ወቅት ጃፓናውያን ሴቶች አብረውት ለመሆን በቁጥር አንድነት የሚመኙት ጎረምሳ ነበር። እሱ ያለበትን ሁኔታ በንቃት ይከታተላሉ፣ ባዩት ቁጥር በደስታ ይጮሀሉ። ስለ ብራድ ፒት ወይም ዴቪድ ቤካም እያወራሁ አይደለም፤ ስለ አበበ ቢቂላ እንጂ። እ.አ.አ በ1961 ዓ.ም በጃፓኗ ኦሳካ ከተማ በተካሄደው የማራቶን ውድድር ላይ ተሳትፎ በአሸናፊነት ካጠናቀቀ በኋላ በጃፓናውያን ሴቶች ልብ ውስጥ መግባት የጀመረው አበበ ቢቂላ በ1964ቱ የቶኪዮ ኦሎምፒክ ለመሳተፍ ወደጃፓን ሲሄድ በሰውነት አቋማቸው ከሚበልጡትና በእድሜ ከሱ ከሚያንሱት ፈርጣማና ጡንቸኛ አሜሪካዊን የኦሎምፒኩ ተሳታፊዎች ቦክሰኛው ጆን ፍሬዠርና ዋናተኛው ዶናልድ አርቱር ሾላንደር ይልቅ የሀገሪቷን ሴቶች ቀልብና ልብ መስረቅ ችሏል።

ቀሪውን ለራሳችሁ እዚህ ይጫኑ:: ሳምንት ሌሎች የኣማርኛ ብሎጎችን ይዤ እቀርባሁ:: ለእንሊዝኛ ቋንቋ አንባቢዎቼ ነገ የእንሊዝኛ ብሎጎች ክለሳዪን ይጠብቁ:: መልካም በአል::

የኢትዮጵያ ጦማሮች ምን ጻፉ?

ይህንን አምድ በጦማሬ ከጀመርኩ ሳምንታት ቢቆጠሩም በአማርኛ ከሚጻፉ ጦማሮች ከማንበብ አልፌ በወፍ በረር ለመከለስ ሀይል ኖሮኝ አያውቅም ነበር። አሁን ግን ሰሞኑን የአማርኛ ጦማሬያን ቈጥር ደስ በሚል ሁኔታ እየጨመረ በመምጣቱ ከዛም ባሻገር የሁለቱ አበይት ጦማሬያን ጦማሮች አቤ ቶኪቻው እና የተስፋዬ ገብረአብ የቅዳሜ ማስታወሻ ጦማሮች ኢትዮጵያ ውስጥ መታገዳቸውን በፌስቡክ በርካቶች በመናገራቸው በትንሹ እነዚህ ሁለት ምን እንዳሉ እንኳ በወፍ በረር ብከልስ አንድ ነገር ነው በሚል ነው::

እሺ ለመግቢያ ያህል ይህቺን ካልኩ በዝህ ሳምንት የብዙ ኢትዮጵያንን ትኩረት ሥቦ ወደ ነበረው ዜና ልሂድ::
በከፍተኛ ሁኔታ ስትደበደብ በፌስቡክ ስለታየችው ህጻን ማን ምን አለ:: ምንም እንኳ የአዲስ ነገሩ መስፍን ነጋሽ ከጦማሬነቱ ይልቅ ወደ ጋዜጠኝነቱ የሚያደላ ቢሆንም በፌስቡክ ገጹ ላይ ያሰፈረው ቀልብ ሳቢ
ማስታወሻ የጉዳዩን ውስብስብነት ሰለሚያስረዳልኝ እንዲህ ጠቅሸዋለሁ:መስፍን ፦

በማንኛውም የዜና ክፍል ውስጥ የዜናን ጭብጥና አንጻር መወሰን፤ ከዚያ ደግሞ “ልዩ” ጥበቃ የሚሹ አካሎችን ፍላጎት ከግምት ማስገባት መደባኛ ሥራ ነው። ግን ከባድና አወዛጋቢ ሊሆን ይችላል። ጉዳዩን ይህ ዜና አስታወሰኝና ማለፍ አቃተኝ። በቅድሚያ ግን ይሀን ሐሳብ የጫርኩት ዜናውን የሠሩትን ባለደረቦቼን ለመክሰስ ሳይሆን በትህትና ለማስታወስ መሆኑ ይታወቅልኝ። ይህን መሰሉ ክርክር ምንጊዜም የሚጠፋ አይደለም።

ይልና:

ለመሆኑ ዜናው ምንድን ነው? የልጅቷ (የተበዳዩዋ) ማንነት መታወቁ ነው ወይስ የእናትየው (የአጥፊዋ) መታወቅ? ጉዳዩን ለዜናነት ማብቃት ተገቢ ውሳኔ ነው እላለሁ። የተመረጠው ጭብጥ እና አንጻር ግን ዜናው ያገለግለዋል ተብሎ የሚታሰበውን ፍላጎት መልሶ የሚጎዳ ይመስላል፤ እርግጠኛ መሆን አይቻልም። ከተራ የወሬ ሱስ ባሻገር ሕዝቡም ሆነ ጋዜጠኛው የልጅቷን ማንነት እንዲያውቅ የሚገፋፋው ሕጋዊ ወይም ሞራላዊ/ማኅበራዊ ምክንያት ምንድን ነበር? ልጅቷን ከነስሟና ከነሰፈሯ በማሳወቅ የሚገኘው ጥቅም ምንድን ነው? ምናልባት ኅብረተሰቡ ወይም የሕግ አካሎች ልጅቷን አውቆ የመርዳት ፍላጎት አላቸው ብሎ መነሳት ይቻላል። ይህን ፍላጎት ለማሟላት የልጅቷን መታወቅ መግለጽ ብቻ (ዝርዝሩን ሸሽጎ) አይበቃም ነበር ወይ? የዚህች ልጅ በዚህ መንገድ መታወቅ እንደሚጠቅማት በምን ማረጋገጥ እንችላለን? (በግሌ፣ በጋዜጠኝነቴ ጭምር፣ ልጅቷ በዜናው እንደምትጠቀም ማረጋገጥ አልችልም፤ ትጎዳም እንደሆነ መገመት እንጂ ማስረገጥ አልችልም።)

ብሎ በገራገር አማርኛው ያሳስበናል:: ሁሉንም ማንበብ ከፈለጉ ከዚህ ይጫኑ::

ከዚሁ ዜና ጋር በተያያዘ ጆናስ የተባለ ጦማሪ “ሜሪን ያየ በካሜራም ሆነ በጌም አይጫወትም!!!” በሚል የተበዳዩዋን ሰቆቃ በሞባይሏ ካሜራ ያስቀረችውን ሜሪ የተባለች ወጣት በፌስቡክ ጓደኞቿ የደረሰባትን ውርጅብኘ እስነብቧል::

የመታገድ አደጋ ገጥሟቸው ወደ ነበሩት እውቅ ጦማሪን ስመለስ አቤ ቶኪቻውን እናገኛለን:: አቤ ጦማሩን በቅርብ የጀመራት ቢሆንም መንግስት የፈራት ይመስላል:: የጎብኚዎቿም ቁጥር ቀላል የሚባል እይደለም 40,316 :ይህንን ያዮ የአቤ ወዳጆችም አይዞህ አቤ በለውታል:: አቤ በዚህ ሳምንት ብዙ አጫጭር ጽሁፎች አስኮምኩሞናል;; የኔን ትኩረት የሳበችው ግን የእነ ሰይፉ ሰይፍ በአሮጊቷ ላይ … ቡጨቃ እና ቁምነገር በሚል የከተባት ናት:: ምክኒያቱም እኔም በዚህ ጉዳይ የተሰማኝን በጦማሬ አስፍሬ ሰለነበር ነው:: በተጩማሪም አትሌት፤ ኃይሌ ገብረ ስላሴ ስለ መምህራን የደሞዝ ጭማሪ ጥያቄ በሰጠወ አስተያየት ፌስቡካውያን እንዴት እንደተማረሩበት በግልጽ ቋንቋ ሰለነገረው:: ሙሉውን ጽሁፍ ከዚህ ያግኙት:: ካልታገድ፡ ኡፋ የሰይጣን ጆሮ አይስማ::

ሌላው ብዚህ ሳምንት ብዙ የፌስቡክ ተጠቃሚዎችን ትኩረት ስቦ በየገጻቸው ሲለጥፉት እና ሲያካፍሉት የሰነበቱት
መታደግ አደጋ ገጥሞት እስካሁንም እንደ አቤ ጦማር ነጻ ያልወጣው የተስፋዬ ገብረአብ የቅዳሜ ማስታወሻ ጦማር ላይ በራሱ በተስፋዬ የተጻፈ “መለስ ዜናዊ! – በማን ይተካል?” የሚል የቀረበ ጽሁፍ ነው::

ተስፋዬ ከስዬ እስከ ሃይሌ ገብረስላሴ መለስ ዜናዊን ሊተኩ ይችላሉ ያላችውን ገለስቦች አሥቀምጧል:: ሃይሌንም ተስፍ እንዳይቆርት በሚመስል “ሃይሊሻ! ለምን አትወዳደርም? የላይቤሪያው ጆርጅ ዊሃ እንኳተወዳድሮአል። ህዝቡ ግልብጥ ብሎ ነው የሚመርጥህ…” ብሎ ወንድማዊ ምክሩን ለግሶታል:: ከከፈተሎ ይህንን ተጨነው ዘና ይበሉት::

በህግ አምላክ!! ደሞዜን በሚል የደሞዙ ያለፍቃዱ ግድብ ለማሰሪያ በሚል መቆረጡ ያሳሰበው አቤል የሚባል ጦማሪ ስጋቱን በጦማሩ እንዲህ ከትቧል:: መራመድና ባሉበት መሽከርከር፤ ሁለት የኑሮ ፈሊጦች በሚል የበፍቄ አለም ጦማር የኢትዮጵያንን የኑሮ እና የእድሜ አበሳ ወ/ሮ ሙሉ የሚባሉ የ33 ዓመት የሥራ ልምድ ያላቸው ዕድሜያቸው ግን 24 የሆነ ሴትን በማሥተዋወቅ በሕይወታችን ስለሚገጥመን ውጣ ውረድ ያሰቀኘበት ጽሁፍ ቢነበብ ቁም ነገሩ አይረሴ ነው:: ሙሉ ጽሁፉን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
በመጨረሻ ግን ደንቅ በሆነ የሰላ አቀራረብ እስክንድር ነጋ ለፍርድ ቤት እራሱን ለመከላከል ያቀረበውን ክርክር በርካታ የፌስቡክ ተጠቃሚዎች ከፍትህ ጋዜጣ ላይ በመውሰድ በየገጻቸው ሲለጥፉት እና ሲያካፍሉት ከርመውል:: መልካም ንባብ